Saturday, May 30, 2020

ስም -አስማት - የመጠሪያ ስም እና የክርስትና ስም



የስመዎ ትርጉም ምን ማለት ነው? የልጆቸዎም ሆነ የእርሰዎ ስሞች ከአባት ስም ጋር ተያይዘው ሲነገሩ ስሕተት ይፈጥራሉ ወይምስ የተስማሙ ናቸው? ለወደፊቱ ስም ማውጣት ሲፈልጉ አውደ ጥናትን ይጎብኙ ቀድመውም ከአውደ ጥናት ይማሩ።
ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን የሚለውን መጽሐፍ ለመግዛት የሚከተለውን ይጫኑ
https://amzn.to/3ciLDAb   ወይም ይደውሉ +1 703 254 6601

ማን ይባላሉ? የስመዎ ትርጉምስ ምን ማለት ነው?
አስማት ምን ማለት ነው?
“አስማተ መለኮት” ይባላል?
አመተ ማርያም? ወይስ ዓመተ ማርያም?
በአውደ ጥናት ነገ በቀጥታ ስርጭት መልሶቹን ያገኛሉ
ከአማዞን ለመግዛት የሚከተለውን ራሱ መጽሐፉን ይጫኑ፤ ወይም በ ይደውሉ +1 703 254 6601 















የክርስትና ስም  እና ትርጉሙ

ኀይለ ሥላሴ
ኀይለ መስቀል
ኀይለ ማርያም
ኀይለ ሚካኤ

ገብረ እግዚአብሔር
ገብረ ሥላሴ
ገብረ ማርያም

አመተ ማርያም
አመተ ኢየሱስ
አመተ ሥላሴ

ወልደ ኢየሱስ
ወልደ ማርያም
ወልደ ገብርኤል

ወለተ ኢየሱስ
ወለተ ማርያም

ፅጌ ማርያም
ፅጌ ድንግል
መዐዛ ማርያም
መዐዛ ድንግል
መዐዛ ሥላሴ
ሥርጉተ ሥላሴ
ሠርጸ ድንግል
ጽርሐ ጽሆን
ወልደ ሰንበት
ሥርጉተ ማርያም
ፀዳለ ማርያም
 እኅተ ማርያም

የመጠሪያ ስም
የመጠሪያ ስም እና የክርስትና ስም
·        በግእዝ
·        በሐምስ
·        በራብዕና
·        በሣብዕ
የሚጨርሱ ስሞች ከአባት ስም ጋር ለመያያዝ አመች ይሆናሉ።
·        በሳድስ
·        በካዕብ
·        በሣልስ
የሚጨርሱ ስሞች ከአባት ጋር አብረው መያያዝ ይኖርባቸዋል ብቻቸውን ስንጠራቸው ግን ሰዋስዋዊ ስሕተትን ይፈጥራሉ።

ለምሳሌ፡
በግእዝ የሚጨርስ ስም ብዙ ጊዜ ግስ ወይም ቨርብ ነው። ለምሳሌ
“አበበ” ግስ ነው ራሱን ችሎም ሊጠራ ይችላል ግን የቃሉ ባሕርይ ስም አይደለም “ግስ” ይባላል፤ “ግስ”ደግሞ የዐረፍተ ነገር ማሠሪያ ነው የሚሆነው፡

“ፍቅሩ” ይህ ቃል “ቅጽል” ነው ስምም ይሆናል፤ ግን ከአባት ስም ጋር ለማያያዝ ሲፈለግ ከሰዋስዋዊ ሕግ ውጭ በሆነ መልኩ ነው የሚያያዘው


“አለሚቱ” አለም የሚለው ቃል “ይህች ዓለም” ማለት ነው። ይህ ቃል ከ አባት ስም ጋር ሲያያዝ ወንድ እና ሴት የሚባል የዐረፍተ ነገር ወይም የግግር መዋቅርን ስለሚያፈርስ “ወንድ እና ሴት” የሚባል የአገባብ ስህተትን ይፈጥራል

No comments:

Post a Comment