Thursday, August 22, 2019

ታሪከ ፍልሰታ፣ ትንሣኤሃ ወእርገታ ለማርያም ድንግል

Filseta, Tinsaeha, we Ergeta Lemariam Dingle Belsane Geez 

ታሪከ ፍልሰታ፣ ትንሣኤሃ ወእርገታ ለማርያም ድንግል




ይህ በያመቱ የሚወጣው የታዋቂ ገጣምያን ግጥሞችን ያሰባሰበ ሲሆን በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የእንግሊዘኛ ግጥሞቼ ታትመው ወጥተዋል።

Ring Video Doorbell with HD Video, Motion Activated Alerts, Easy Installation - Satin Nickel click to buy


Atomic Habits: An Easy & Proven Way to Build Good Habits & Break Bad Ones 

“ወብዙኃተ ካልኣተ ተአምራተ ገብረ እግዚእ ኢየሱስ በቅድመ አርዳኢሁ ዘኢተጽሕፈ ውስተ ዝንቱ መጽሐፍ” ወንጌለ ዮሐንስ 20፡ 30
“ወኵሉ መጽሐፍ ዘበ መንፈሰ እግዚአብሔር ተጽሕፈ ይበቁዕ ለኵሉ ትምህርት ወተግሣጽ ወአርትዖ ወጥበብ ወጽድቅ ከመ ይትገሠጽ ብእሴ እግዚአብሔር ውስተ ኵሉ ምግባረ ሠናይ” መልእክተ ጳውሎስ ካልእት ኀበ ጢሞቴዎስ ሣልሳይ ምዕራፍ ወኁልቍ ዐሠርቱ ወስድስቱ እስከነ ዐሠርቱ ወሰብአቱ።
ታሪከ ፍልሠተ ሥጋሃ ለማርያም ድንግል።

ቅድመ ኵሉ ነገር ይደልወነ ናእምር ትርጓሜሁ ለፍልሰት፤ ፍልሰት ብሂል ስደት፤አው ሑረት፤ ሶብ አሐዱ ነገር አው አካል ይሰደድ አው ይትወሰድ እምነ መካን ዘነበረ ቅድመ ኀበ ካልዕ ወሐዲስ መካን ንጸውኦ “ፍልሰት”
ወአመ ንቤ “ፍልሰታ” ንትናገር በይነ ፍልሰተ አሐቲ አንስታይ ፆታ፤ አላ ኢነአምር ዘመኑ ውእቱ ዝንቱ ፍልሰት፤ ኩለሔ ይደሉ ከመ ንጽሐፍ ከመ ዘይተሉ ዐረፍተ ነገር  “ፍልሰታ ለማርያም” አው ፍልሰተ ሥጋሃ ለማርያም” ዝንቱ ዐረፍተ ነገር ይነግረነ በይነ ፍልሰተ ሥጋሃ ለማርያም አው በእንተ ፍልሰታ ለማርያም፤ በይነ ፍልሰተ ሥጋሃ ለማርያም እምነ ብሔረ ሕያዋን ኀበ ጌቴ ሴማኒ።

በዝንቱ ትምህርትነ ነሐትት ወንትሜሀር በይነ ታሪከ ድንግል ማርያም፤ ወፆመ ሐዋርያት ቅዱሳን ወኀይለ ጸሎት ዘይጼለይ በእምነት ጽንእት እንተ አልባቲ ኑፋቄ። ዝንቱ ታሪክ ያርእየነ ከመ እግዚአብሔር ሰማኤ ስእለት ወተወካፌ ጸሎት ውእቱ፡

ጸሎት ብሂል ልሣነ አምላክ ወሰብእ እለ ይትናገሩ በበይናቲሆሙ፤ ወኵሉ ሰብእ ይደልዎ ከመ ይጼሊ ወትረ ኀበ አምላኩ እስመ አልቦቱ ሐብት፤ ጥኢና፤ ወሰላም እምኔሁ (እምነ ርእሱ) ። ወበእንተዝ ይደልዎ ይጤይቅ ኵሎ ነገረ እምነ አምላኩ። ንሕነሰ ነዳያን ወአልብነ ምንተ።

 አመ ነሐስስ ሰላመ ንጠይቅ ሰላመነ  እምኔሁ ወአመ ነሐምም  ንጠይቅ ጥኢናነ እምኔሁ፤ ወአመ ንርህብ ንጠይቅ እምኔሁ መብልአ፤ ወውእቱሰ ይሁበነ በፍቅር ኵሎ ዘነሐሥሥ።

በከመ ይቤሉ መጻሕፍተ ብሉያት ወክርስቶስ በወንጌሉ ኵሉ ሰብእ እመ ይጤይቅ አምላኮ እንዘ ይጼሊ እምልቡናሁ ምስለ አሚን ርትዕት ወጽንእት ይረክብ ዘየሐሥሥ ወዘይጤይቅ።

እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየደ ኪዳነ ምስሌነ ወምስለ ኵሎሙ ተላውያኒሁ ዘይስእለዎ አው ዘይጤይቅዎ በጸሎት ምስለ አሚን እንተ አልባቲ ነቅዕ።
ኦ ምእመናን! ነጽሩ ኀበ ዝንቱ ቃለ ክርስቶስ ዘተናገረ በወንጌለ ማቴዎስ በሳብዓይ ምዕራፍ ከመ ዘይተሉ።

“ሰአሉ ወይትወሀበክሙ ኅሡ ወትረክቡ፤ ጎድጉዱ ወይትረኀወክሙ እስመ ኵሉ ዘሰአለ ይነሥእ ወዘሂ ኀሠሠ ይረክብ ወለዘሂ ጎድጎደ ይትረኀዎ..” ማቴ 7፡7
ዝንቱ ውእቱ ቃለ ክርስቶስ ዘኢየሐልፍ ወንሕነ ነአምን ቦቱ ለእመ ንጼሊ በልቡና ንፁህ ወበአሚን ምሉእ ንክህል ከመ ናፍልስ ደብረ! ወአልቦ ነገር ዚኢይትከሐል በጸሎት።

ዝንቱ ውእቱ ምክንያተ ጾመ ሐዋርያት ወውእቶሙ የአምሩ ዘንተ ከመ እግዚአብሔር ይገብር ሎሙ እለ ይስእሉ እምኔሁ፤ ያጸምእ ጸሎቶሙ ወያወስእ ጥያቄሆሙ  ወበእንተዝ ጾሙ ከመ ይንስዑ ሥጋሃ ለማርያም ድንግል ዘሐሠሡ፤ እስመ እግዚአብሔር ተናገረ በመጻሕፍቲሁ በይነ ኃይለ ጸሎት ወእምነት።

ሐዋርያት ጾሙ ክልኤተ ሱባኤያተ አው አሠርተ ወአርባእተ ዕለታተ እንዘ ይዌጥኑ እም አመ አሚሩ ለነሐሴ እስከነ አሠርቱ ወአርባእቱ ለነሐሴ. ወአመ ፈጸሙ ሐዋርያት ሱባኤሆሙ አቀበ እግዚአብሔር ቃሎ ዘተናገረ ወተወክፈ ጸሎቶሙ ለሐዋርያቲሁ ወወሀቦሙ  ሥጋሃ ለማርያም ድንግል ዘይሐሥሡ፤ ወሐዋርያት አእረፉ ሥጋ በክብር በጌቴ ሴማኒ ወበ ሰሉስ ዕለት ተንሥአት ከመ ትንሣኤ ወልዳ ወአርገት ከማሁ መንገለ ሰማይ በክብር። 

ወናሁ እነግረክሙ በይነ ዕድሜሃ ወሕይወታ ለማርያም ድንግል እመ አምላክ በዝንቱ ዓለም፤ እግዝእተነ ማርያም ተጸንሠት አመ ሰብኡ ለነሐሴ እምነ አቡሃ ኢያቄም ወእማ ሐና፤ ወተወልደት  አመ አሚሩ ለግንቦት በሐምሣ ወአርባዕቱ ምዕት ሰማንያ ወስድስቱ ዓ/ዓ ።

 አምጣነ ይእቲ ተወልደት በስእለት ወበእንተዝ አመ ኮና ሠለስተ ዓመታ አቡሃ ወእማ ወሰድዋ ኀበ ቤተ መቅደስ አመ ሰሉሱ ለታህሣስ ለትትለአክ በቤተ እግዚአብሔር ከመ ይፈጽሙ  ቃሎሙ ዘተናገሩ እምቅድመ ይለዱ ኪያሃ።

 ወማርያም ድንግል ነበረት አሠርተ ወክልኤተ ዓመታተ እንዘ ይናዝዝዋ መላእክት ወትትልአክ በቤተ መቅደስ በከመ ይቤ መጽሐፍ ወእንዘ ትፈትል ወርቀ ወሜላተ። በከመ ተጽሕፈ በወንጌል አብሠራ መልአክ ዘስሙ ገብርኤል በከመ ተሐርየት ወተሌለየት እምነ ኵሎን አንስት ዘደቂቀ አዳም ከመ ይትወለድ እምኔሃ አምላክ በሥጋ ከመ ያድኅን ደቂቀ አዳም እምኃጢአቶሙ።

እግዝእትነ ማርያም ነበረት በቤተ መቅደስ እስከነ በጽሐት መጠነ አንስት ወሶበ ልሕቀት  ወኮና አሠርተ ወሐምስተ ዓመተ ተጋብዑ ካህናተ ቤተ መቅደስ ከመ ይጠይቁ ፈቃደ እግዚአብሔር ወይርከቡ ላቲ አቃቤ  ወበ ፈቃደ እግዚአብሔር ረከቡ በከመ ተመነዩ ወተውህበት  ለዮሴፍ አምጣነ በጽሆ ዕፃ ከመ ይዕቀባ ወነበረት በቤተ ዚአሁ ተሠዐተ አውርሃ ወሐምስተ ዕለተ።

ወበጽሐ ጊዜ ወሊዶታ ሖረት ኀበ ቤተልሔም ምስለ ዮሴፍ፤ ወሰሎሜ ከመ ይጸሐፉ በትዕዛዘ ንጉሥ በበ ሐገሮሙ ወነበሩ በህየ እስከነ ወለደት ወልደ ዘበኵራ በውስተ ጎለ እንሥሳ ዘቦ በቤተልሔም።

ወበከመ ይቤ ወንጌል ተውህበት ለፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ እንዘ ሀሎ ክርስቶስ በዕፀ መስቀል ከመ ትኩን እመ ኵልነ ወንኵን ንሕነ ደቂቀ ዚአሃ በቃለ ክርስቶስ “ነዋ ወልድኪ ወነያ እምከ” ወነበረት አሠርተ ወሐምስተ ዓመታተ በቤተ ዮሐንስ፤ ወአመ ኮነ ዕድሜሃ ስድሳ ወአርባእቱ ዓመታተ፤ አመ ዕሥራ ወአሚሩ ለጥር በዐርብዓ ወሰመንቱ ዓመተ ምሕረት አዕረፈት እምዝንቱ ዓለም፤ በከመ ተጽሕፈ በመጻሕፍት ወመላእክት አእረፉ ሥጋሃ በብሔረ ሕያዋን በታሕተ ሥርወ ዕፀ ሕይወት እስከነ አሠርቱ ወአርባዕቱ ለነሐሴ።

ከመ ነበብኩክሙ በማዕከለ ዝንቱ ትምህርት ወሶበ ፈጸሙ ሐዋርያት ክልኤተ ሱባኤያተ እስከነ  አሠርቱ ወአርባእቱ ለነሐሴ  ተወክፉ ሥጋሃ ዘሐሰሱ በጸሎት ወአእረፍዎ ለሥጋሃ በጌቴ ሴማኒ ወበሳልስት ዕለት ተንሥአት ወአርገት ከመ ወልዳ ዋሕድ።

ወበእንተዝ ናከብር በዛቲ ዕለት ሠለስተ በአላቲሃ ለማርያም ዘይሰመያ ፍልሰተ ሥጋሃ፤ ዕርገታ ወትንሣኤሃ ። አበው ወአኃት በዝንቱ ጾም ረከቡ ሐዋርያት ዘሐሰሱ ወዘ ተመነዩ፤ እምነ አምላኮሙ፤ ወበእንተዝ ይደልወነ ንጤይቅ ርእሰነ ወንሕትት ግብራቲነ፤ ኵለሄ ንጸውም ወንጼሊ አላ ኢይሰምአነ እግዚአብሔር፤ ወኢንረክብ ዘነሐስሦ፤ ኢይመይጥ እግዚአብሔር እዝነ ምሕረቱ ኀበ ጽራህነ፤ ወኀበ ጸሎትነ።

በከመ ይቤ በመጻሕፍት “ስማይ ወምድር የሐልፍ ወቃልየሰ ኢየሐልፍ” ኢይዌልጥ እግዚአብሄር ቃሎ ዘተናገረ ወውእቱ ወሀበነ ቃሎ  እንዘ ይብል  “ሰአሉ ወይትወሀበክሙ፤ ጠይቁ ወትረክቡ፤ ጎድጉዱ ሆኃተ ወይትረኀው ለክሙ” አላ ለምንት ኢንረክብ ንሕነ ዘንስእል?  ወለምንት ኢይትወሀበነ ዘንጤይቅ? ወኢይትረኀው ለነ ኆኃተ ምሕረቱ? አብያተ ዚአየ ወምክንያቱሰ ቀሊል ወሐጺር! ጾምነ ወጸሎትነ አኮ ከመ ጾም ወጸሎት ዘያሠምሮ ለእግዚአብሔር፤ ወበእንተዝ ንነስህ ወንእመን ከመ አበስኖ ለአምላክነ ወንትመየጥ ኀበ ምግባረ ሠናይ ወናርትዕ ፍኖተነ ምስሌሁ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አምላክነ በይነ ዘአብጸሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት አቂቦ በምሕረቱ፤፡

ጸሎታ ወበረከታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ይህድር በላእሌነ 

Monday, July 29, 2019

Preaching in Geez Languge/ስለ ቅዱስ ሐምሌ 19 የቅዱሳን በአል ስብከት በግእዝ ቋንቋ በመ/ር መላኩ



ስብከት በይነ ተራድኦተ መላእክት ወጽንአተ እምነተ ቅዱሳን ወኀይለ እምነት በውስተ አማንያን በመ/ር መላኩ

ቪዲዮም የድምፅ ጥራቱ ተስተካክሎ እንደገና የተዘጋጀ ነው

Sunday, July 28, 2019

Preaching in Geez Language about Hamle Gabriel/የሐምሌ ገብርኤል ስብከት በግእዝ ቋንቋ ...


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ 
አምላ
ሊቃውንት፤ ካህናት፤ ዲያቆናት ምእመናን አበዉ ወአኀው እማት ወአኀት ኵልክሙ በሐክሙ እብል በስመ እግዚአብሔር ወእግዚአብሔር ይሰባሕ በይነ ዘአብጽሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት አሜን።

ዮም በዛቲ ዕለት በፈቃደ እግዚአብሔር ንትሜሀር በይነ ተራድኦቱ ለቅዱስ ገብርኤል መልአክ ወክልኤቱ እም ወሕጻን ሰማዕታት ዘይሰመዩ ቅርቆስ ወኢየሉጣ፡ እለ ናከብር ሎሙ ዝክረ በአሎሙ  ዓመ ዐሠርቱ ወ ተሰዓቱ ለሐምሌ በበ ዓመቱ እስመ በዛቲ ዕለት ውእቶሙ ኮኑ ሰማዕተ በሐገረ ሮሜ።

 በዝንቱ በአል ንሐትት ሕየንተ ታሪክ ዘይሰመይ ዘመነ ሰማዕታት ወዘተፈጸመ ቅድመ እሥራ ምዕት ዓመተ ምህረት።

ዝንቱ ዘመን እምዐሠርቱ ምዕት ወስድሳ እስከነ ሠለስቱ ምእት ዐሠርቱ ወክልኤቱ ዓ/ም ድኅረ ክርስቶስ ውእቱ፤ ወንጼውኦ  “ዘመነ ሰማዕታት” አው “ዘመነ ስደት” ብሒለነ፤ እስመ በዝንቱ ዘመን ብዙኃን ክርስቶሳውያን ተሰዱ ወተቀትሉ በአላውያን ነገሥታተ ሮም፤ በእንተ ዘአምኑ በክርስቶስ ወሰምዑ ክርስቶስሃ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ፤ ወተሰይሙ በስሙ ተብሒሎሙ “ፆታ ክርስቶስ”።

 ወነገሥታተ ዝንቱ ዘመን አው ነገስታተ ሮም እንዘ ያቀውሙ ጣዖታተ በስሞሙ ወበ መልክኦሙ፡ ወአዘዙ ኵሎሙ ዘይነብሩ በታሕተ ሥልጣኖሙ ከመ ይስግዱ ለጣዖታት ዘአቀሙ በስሞሙ ወያምልክዎሙ።

በከመ አለበውኩክሙ በሙባአ ትምህርትየ በዝንቱ በአል ንትሜሀር በይነ ተራድኦተ አሐዱ መልአክ ዘስሙ ገብርኤል ወበይነ ኀይለ እምነት በኀበ አማንያን ከመ ኢየሉጣ ወቂርቆስ ዘይመስሉ አው ከመ ክልኤቱ ሰማዕታት፡፡

ሰማዕት አው ሰማዕታት ቢሂል ሰብእ ዘተቀትለ በይነ ዘተናገረ ጽድቀ በእንተ ክርስቶስ አው በእንተ አሚን በክርስቶስ ቅድመ አላውያን ነገሥታት። አው ብእሲ ወብእሲት እለ ተቀትሉ በይነ ዘተናገሩ ጽድቀ በእንተ ክርስቶስ በቅድመ አላውያን እንበለ ይፍርሁ ሞተ ሥጋ።

በከመ ይቤ ጳውሎስ በመልእክቱ ኀበ ዕብራውያን፤ መላእክት ውእቶሙ መናፍስት ዘኢይትገሠሱ ወዘኢይትረአዩ በአካለ ሥጋ ወግብሮሙሰ ዘይትፌነዉ እም ኀበ እግዚአብሔር ለተራድኦት ወለአቂቦት ኪያነ ዘነአምን ክርስቶስሃ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ። “አኮኑ ኵሎሙ መላእክት መንፈስ እሙንቱ ወይትፌነዉ ለመልእክት በእንተ እለ ሀለዎሙ ይረሱ ሕይወተ ዘለዓለም” ። ዕብ. 1፡14

ቅድመ እትናገር በይነ ታሪከ በአል ዘዮም መፍትው እንግርክሙ በእንተ ቅዱስ ገብርኤል ዘይሰመይ በአፈ ሊቃውንት ከመ ኮነ ሰባኬ ቃለ እግዚአብሔር  ወመጋቤ ሐዲስ በቅድምና፤ ወበእንተዝ ነአምሮ ለገብርኤል መልአክ በአበይት ተአምራት ሠለስቱ፡
ቀዳማይ ተአምር፡ ውእቱ ገብርኤል ወጠነ ትምህርተ ስብከት፡ ወሰበከ መላእክተ በዓለመ መላእክት በዕለተ ሰንበት እንዘ ይብል “ንቁሙ በበ ሕላዌነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ” ወሰበኮ ለዝንቱ ስብከት ሶበ ተሀውኩ መላእክት በክህደተ ሳጥናኤል መልአክ አመ ይቤ “አነ ፈጠርክዋ ለዛቲ ዓለም ወፈጠርኩ ኪያክሙ አልቦ ካልእ ፈጣሪ ዘእንበሌየ”

ካልአይ ተአምር ፡ ገብርኤል ተፈነወ ፍጡነ እም ኀበ አምላኩ ከመ ይርድኦሙ ለዳንኤል ነቢይ ወለሠለስቱ ደቂቅ በአጺዎተ አፈ አናብስት ወበአጥፍኦተ እሳት ከመ ኢይሙቱ እንበለ ኃጢአቶሙ ወይትአወቅ ኀይለ እምነት ጽንእት። ወበዝንቱ ተአምር ብዙኃን ተመይጡ እምነ አምልኮ ጣኦት ወአምኑ በአምላከ ዳንኤል ወበሰለስቱ ደቂቅ

ወሣልስ ተአምር ፦ ገብርኤል ተፈነወ እምነ አምላኩ ኀበ ድንግል ወቅድስት ማርያም እመ አምላክ ከመ ያብሥራ ወይንግራ ምሥጢረ ሥጋዌ ወከመ ተሐርየት ለከዊነ እመ አምላክ። “ተፈሥሒ ፍሥሕት ኦ ምልእተ ጸጋ እግዚአብሔር ምስሌኪ ወቡርክት አንቲ እምአንስት …”

ወራብዕ ተአምር፡ ገብርኤል አቍረረ ፍሉሐ ማየ፦
 ከመ መጽሐፈ ገድሎሙ ለቅድስት ኢየሉጣ ወቅዱስ ቂርቆስ ይቤ ሐገረ ኢየሉጣ ይትበሐል አንጌቤን ወዝንቱ መካን ውእቱ አድያም ዘሐገራት እለይትቀነዩ በታህተ ነገሥታተ ሮም። ወዝንቱ ዘመን ዘመነ አላውያን ውእቱ።

 ወአመ ኮነ ዕድሜሁ ለቂርቆስ ሠለተ ዓመተ ተጸውአት ኢየሉጣ ኀበ መኮንነ ሐገር ወተጠየቀት በእንተ አምልኮተ ጣዖት ወአውሥአቶ ወትቤሎ ኦ መኮንን ሀሎ ሕጻን ዘሠለስቱ ዓመት መዋዕሊሁ፤ ተሰአል ኪያሁ።

ወመኮንን ፈነወ ሐራሁ ኀበ ሀሎ ሕጻን ቂርቆስ ወሐራ ረከቦ ለቂርቆስ ሕፃን አብጽሆ ኀበ መኮንን፤ ወመኮንን ይቤሎ ለሕጻን በሐከ ኦ ፍሡሕ ሕፃን፤ ወነበቦ በእንተ አምልኮተ አማልክቲሁ፤

ወአውስአ ቂርቆስ በመንፈሰ እግዚአብሔር ወረገሞሙ ለንጉሥ ወለመኳንንቲሁ ወለአማልክቲሁ እስከ ይደነግፁ ኵሎሙ እለሀለዉ መስለ መኮንን ።

ወተምአ መኮንን ወአዘዘ አግብርቲሁ ከመ ይደዩ ማየ ውስተ ዐባይ ጽሕርት ዘብርት ወያፍልሕዋ ውስተ እሳት ወኮነ ድምጸ ፍልሐታ ለጽሕርት ከመ ነጎድጓደ ክረምት። ወይቤ ቅዱስ ያሬድ “ድምጻ ለጽሕርት ከመ ነጓድጓደ መብረቅ”

ሕፃን ወእሙ ሶበ ቦኡ ውስተ ጽሕርት እንዘ ይሠምዑ ክርስቶስ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ ፍጡነ መጽአ መልአከ እግዚአብሔር ዘስሙ ገብርኤል ወአቁረሮ ለኃይለ እሳት ። በከመ ተጽሕፈ በኦሪት ዘከመ ፈነወ መልአኮ ወአድኀኖሙ ለሠለስቱ ደቂቅ እምእሳት ዘይነድድ፤ ወገብረ ከማሁ በኢየሉጣ ወቂርቆስ ፍቁራኒሁ ወዘተአመኑ ቦቱ።
ናሁ ንትመየጥ ኀበ ርእስነ ወንሕትት ልቡናነ። ዘፈነወ መልአኮ ወአድኀኖሙ ለዳንኤል፤ ወለሰለስቱ ደቂቅ ወለ ኢየሉጣ ወቂርቆስ ውእቱ እግዚአብሔር ዘትማልም ወዮም፤ ወናሁ ይረድአነ ወያድኅነነ አላ መፍትው ብነ እምነት ዘአልቦ ነቅእ ወዘአልቦ ፍርሃት።

በዝንቱ ዘመን ዘመነ ዚአነ ንሬኢ በዐይንነ ለዘሰማዕኖ በእዝንነ፤ ብዙሐን ይትቀተሉ በሰቂል፤ በሰይፍ፤ በእሳት፤ እንዘ ንሬእዮሙ በብንተ ዐዕይንቲነ። ወበእንተ ዝንቱ መፍትው ንጼሊ ወንመይጥ ልቡናነ ኀበ እግዚአብሔር ከመ ይሚጥ ዐዕይንተ ምሕረቱ ኀቤነ ወኀበ ሐገሪትነ ኢትዮጵያ። ወይፈኑ ለነ መልአኮ ከመ ያቁርር እሳተ ዘይነድድ በውስቴትነ።

እግዚአብሔር ለብዎቶ የሐበነ ወያኅድር በልቡናነ ለዘሰማእኖ ወያፍሪ ፍሬ ሠላሣ ስድሳ ወምዕተ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Sunday, July 7, 2019

ስብከት በልሣነ ግእዝ በመ/ር መላኩ አስማማው /Preaching in Geez Language by M/r Melaku A...



ስብከት በልሳነ ግእዝ


መጻሕፍቱን ለመግዛት የመጻሕፍቱን ከበር ይጫኑ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን።
አበውየ ካህናት ወአኀውየ
ዲያቆናት፤  አኀትየ ወእማትየ ተለውተ ክርስቶስ ኵልክሙ እፎ ሀደርክሙ
ወእፎ ሀሎክሙ?
አምላክነ ሔር ወመስተሣህል ውእቱ በይነ ዘአብጸሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት ዘእንበለ ይዝክር አበሣነ ዘንገብር
በተናግሮ ፤ በሐልዮ ወበገቢር በበዕለቱ ወበበ ሰዓቱ። ወበእንተ ኵሉ ዘገብረ ወዘይገብር ለነ ይሰባሕ ስሙ ለእግዚአብሔር አምላክነ።
ከመ ፈቃደ እግዚአብሔር ዮም ንትሜሀር በይነ ተዋሕዶትነ በዋሕድ አምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ዘወሀበ ነፍሶ ለቤዛ ኵሉ ዓለም።

ወርእሰ ትምህርትነሰ ውእቱ ዘይትረከብ እመነ መዝሙረ ዳዊት በአሐዱ ምዕት ሠላሳ ወክልኤቱ መዝሙር
በቀዳማይ ኍልቁ ወይብል ከመዝ

“ ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ” መቅድመ ኵሉ ነገር ይደልወነ ከመ
ናእምር እሙነ ለርእሰ ትምህርት ዘንትሜሀር።

 ወበእንተዝ ለብዉ ኀበ ዝንቱ ቃል! እንዘ እተረጉም ለክሙ በቀሊላን ቃላት
ከመ ታእምሩ ምሥጢሮ ወመልእክቶ ለዘተነግረ።
ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ ብሂል፤

 አመ  ዕደው ወአንስት አው ሕዝበ እግዚአብሔር  ይትረከቡ በፍቅር ኅቡረ በአሐዱ መካን ወበ አሐዱ ልብ። ነቢየ እግዚአብሔር
ቅዱስ ዳዊት በዝንቱ ምንባብ ኢተናገረ በይነ ሰብእ አው ሕዝብ ዘይነብሩ በአሐዱ መካን አላ ዘአልቦ ውሕደት ውስተ ልቦሙ።
 ውእቱ ይቤ በይነ ሕዝበ እግዚአብሔር
ኵሎሙ በይነ እደው ወአንስት እለ ተዋሐዱ በፍቅር፤ እለ ይነብሩ በአሐዱ መካን፤ እለ ይትናገሩ አሐደ ቃለ፤ በአሐዱ ልብ።

በዝንቱ ዘመን ዘመነ ዚአነ ብዙሐን ይነብሩ ኀቡረ በአሐዱ መካን፤ አላ አልቦ ፍቅር በልቦሙ፤ አልቦ
ውሕደት በቃሎሙ።  ኢንሰይሞ ሠናየ ለዝንቱ ኅላዌ ወለዝንቱ ሕብረት
ዘአልቦ ውሕደተ ልቡና።

ናሁ ንኔጽር ኀበ ርእስነ ወአነ እጤይቀክሙ ወእጤይቅ ርእሰየ በዘይተልዉ ጥያቄያት
ንነብርኑ ምስለ ብእሲትነ አው ብእሲነ፤ ምስለ ደቂቅነ አው ምስለ አዝማዲነ በአሐዱ ቤት፤ በአሐዱ
መካን? ኦሆ ነነብር፤ኦሆ ተዋሐድነ በመካን፤ ተዋሐደን በአካለ ሥጋ።  ዝንቱሰ እሙን ውእቱ። አላ ይነብሩኑ ኅቡረ አልባቢነ? ንትናገርኑ አሐደ ቃለ?
ይትረከብኑ ፍቅር እንተ አልቦቱ ምክንያት በማዕከሌነ? ንትፋቀርኑ በበይናቲነ?

ለእመ ናወሥእ እሎንተ ጥያቄያተ በብሒለ ኦሆ፤ ንክህል ከመ ንብል ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ንሄሉ
ንሕነ አኀው ወአኃት ኅቡረ።
አላ ለእመ ናወሥእ እሎንተ ጥያቄያተ በብሂለ “አኮ” መፍትው ንብል አኮ ሠናይ ወአኮ አዳም ሶበ ንሄሉ
ኅቡረ በመካን ባሕቲቱ፤ አኮ በልብ ወበተፋቅሮ።

መኑመ ኢይነብር ባሕቲቶ በአካለ ሥጋ በዝንቱ ዓለም፤ ወምክንያቱሰ ሰብእ ኢይክህል ነቢሮተ ባሕቲቶ
ወይደልዎ ይገብር ግብረ ምስለ ሰብእ ከመ ይብላእ ወይስቲ፤ አላ ይክህል ይንበር ባሕቲቶ በልቡናሁ፤ እንበለ ያፍቅር ካልአነ  እስከነ የሐልቅ ዕድሜሁ በምድር።

አዝማድየ አጽምዑ በእዝነ ልብክሙ ወአኮ በእዝነ ሥጋክሙ ወነጽሩ በዓይነ ኅሊናክሙ ወአኮ በዓይነ ሥጋ
ክሙ። አምላክነ ይብለነ በቃሉ ሕያው ዘይተሉ።

“ ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ” ወንጌለ ዮሐንስ ምዕራፍ
14 (ዐሠርቱ ወአርባዕቱ)፡ ኍልቁ ዐሠርቱ ወሐምስቱ(15) ። በከመ ሰማእክሙ አምላክነ ይኤዝዘነ ከመ ንግበር አው ንእቀብ ትዕዛዞ።

ምንት ውእቱ ትእዛዙ ለእግዚአብሔር? ትክህሉኑ ትንግሩኒ? ምንተ አዘዘነ ከመ ንግበር?
ውእቱ አዘዘነ ከመ ንትፋቀር በበይናቲነ፤ ወከመ ንንበር አው ንሄሉ በተፋቅሮ ወንትዋሐድ በዘንትናገር
ወነኀሊ በአሐዱ ልብ  ከመ ናክብር ኵሎ ሰብአ እንበለ ናድሉ ለገፀ
ሰብእ። ወንትራዳእ በበይናቲነ፤

አበው ወአኀት፦ አመ ታነብቡ ወትሰምዑ ቃለ እግዚአብሔር

ነጽሩ በዓይነ ሕሊናክሙ
ወአኮ በዓይነ ሥጋክሙ፤ ወአጽምዑ በእዝነ ልቡናክሙ ወአኮ በእዝነ ሥጋክሙ። ኢይሰምእ እዝነ ሥጋ እንበለ እዝነ ልቡና አው ተሌልዮ
እምነ እዝነ ልቡና፤ ወኢይሬኢ ዓይነ ሥጋ ዘእንበለ ዓይነ ኅሊና አው ተሌልዮ እምነ ዓይነ ኅሊና።፤ ዓይነ ሥጋ ወዕዝነ ሥጋ  ባሕቲቶሙ ኢይክሉ  ከመ ይግበሩ ምንተ ዘእንበለ ይትዋሐዱ ምስለ ዕዝነ ውሳጤ ወዓይነ ውሳጤ።

አበው ወእማት፤ አኀው ወአኀት፤ ከመ መጻሕፍት ይሜህሩነ ኵለሔ ኢንነብር ሕያዋነ ወአልብነ ጊዜ በዝንቱ
ዓለም፤ ወሐጺር ውእቱ ዕድሜሁ ለደቂቀ አዳም አቡነ። ወበእንተ ዝንቱ ንመውት ፍጡነ በዘኢነአምራ ቅጽበተ ሰዓት።
“ወመዋዕለ ዓመቲነ ሰብዓ ክራማት እመሰ በዝኀ ሰማንያ ዓም”
መዝሙር 89(ሰማንያ ወተሰዐቱ)

በከመ ይቤ ዳዊት በዝንቱ ዓለም ኢንሄሉ ነዊሐ መዋዕለ፤ ወበእንተዝ ነገር ይደልወነ ንሕንጽ ቤተነ
በመንግሥተ እግዚአብሔር፤ ዝንቱ ዓለም ተውሕበ ለነ ለጊዜሁ ከመ ንሕንጽ ቦቱ ቤተነ ዘልዓለማዌ።

ከመ ተአምሩ ኵልክሙ በዝንቱ ዘመን መኑመ ኢይነብር መጠነ ኍልቆ መዋዕል ዘተጽሕፈ በመዝሙረ ዳዊት፤
ብዙኀን ይመውቱ ቅድመ ሠላሣ መዋዕለ ዓመቲሆሙ። በይነዝ ይደልወነ ንንበር ድልዋኒነ።

እንዘ ንነብር በአካለ ሥጋ በዝንቱ ዓለም ወበዝንቱ መካን መፍትው ንኵን ኅቡራነ ወውሑዳነ በፍቅር
በአሐዱ ቃል ወበአሐዱ ኅሊና። ከመ ነገርኩክሙ ቅድመ በማዕከለ ትምህርትነ ኢንትዋነይ በሕይወትነ ወኢንቅትል ጊዜነ ዘበ ምድር እንተ
ጸገወነ እግዚአብሔር እንበለ ንዋይ እንዘ ንገብር ግብራተ እለ አልቦሙ ረብሕ።

ንሌቡ ፍጡነ ቅድመ ይንሥአነ ሞት እምቅድመ ንሕንጽ ቤተነ ዘበሰማያት።

እስመ ውእቱ መሐሪ ወመስተሣህል ይሐበነ ዐዕይንተ አእምሮ ወለብዎተ ቃሉ ዘሰማዕነ ከመንግበር ሠናየ
ወይሐበነ ዘመነ ንስሐ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እምነ አውደ ጥናት ዘግእዝ
በመ/ር መላኩ አስማማው ቢሰጠኝ

Tuesday, June 25, 2019

የጭንቅ ሰቆቃ/ The Depression of Tragedy-Poem


የጭንቅ ሰቆቃ


አንተ ቸር ፈጣሪ አልፋና ዖሜጋ
ሰላም የባሕርይህ ይቅርታም ካንተ ጋ
ነውና ወደ እኛ ቀኝ እጅህን ዘርጋ፤
ሰብሳቢ የሌለው የባዘነ መንጋ
ሆነን በሜዳ ላይ ቀርበናል ላደጋ።

የኃያላን አምላክ የነገሥታት ጌታ
ፈጥነህ ድረስልን እንዳንንገላታ፤

ልባችን ኮብልሎ ከአንተ ሸፍተን
ብዙ ተንገላታን ለረጅም ዘመን፤
የጥበብ ባለቤት መሆንህን ዘንግተን
በምድራዊው እውቀት ስንመካ ቆየን፤
በታንክ በመትረየስ ስናምን በይፋ
እየከዳን ሄደ እየጣለን ጠፋ፤
ያመኑት ሲከዳ ዋ! ታላቅ አበሣ
ወዳጅ ጠላት ሆኖም ሊበላን ተነሣ።

ተጣላን፣ ተብላላን፣ ተገዳደልንሣ!
ምነው አእምሮ አጣን ሆን እንደ እንስሣ! ።

ኀያሉ ፈጣሪ የሰላሙ ጌታ
ኢትዮጵያን ታደጋት ሁንላት መከታ
ወዳንተ እየጮኸች ቃሏን አሰምታ
ማረኝ ትልሃለች እጆቿን ዘርግታ
ዕንባን እያነባች ጸሎቷን ሳትገታ
ደምን ታለቅሳለች ከጧት እስከማታ።

የዘረኞች ክፋት የክፉዎችም ኃል
ከቦ ሲያጣድፋት ሲጎዳት በከፊል
አምላክ ሆይ ገላግላት የምጥ ጣር ይዟታል።

ፈጣሪ በሰጠሽ በቃል ኪዳንሽ
አመጸኛውን ሰው ስምኦንን ያዳንሽ
በዚያው ታላቅ ፀጋሽ በጽኑ ምልጃሽ
ዛሬም በዚህ ዘመን ማልደሽ ልጅሺን
አድኛት ታደጊያት እናት ኢትዮጵያን።

እምዬ ኢትዮጵያ ውቢቷ ሐገሬ
ዘመን ጣለሺና ጠወለግሽ ዛሬ
በልጆችሽ ኀዘን ኑሮሽ ስለከፋ
መልክሽ ተለውጦ ውበትሺም ጠፋ።

በአንበሦች ጉድጓድ እንደሚል መጽሐፍ
ዳንኤልን ያዳንክ ሕይወቱ ሳያልፍ
ኢትዮጵያን አድናት፣ ታደጋት፣ ከገዳዮች ሰይፍ።

ፈጣሪ ሆይ እርዳት ስማት በጽሙና
እምዬ ኢትዮጵያ ተጨንቃ በጠና
ከሞት አፋፍ ሆና ትጣራለችና።

ኢትዮጵያ ተናዘዥ ኃጢአትሺን ንገሪ
ለሊቀ ካህናቱ ለዓለም ፈጣሪ፣
ንስሐ ከገባሽ ምንም ሳትሠውሪ
እርሱ ያድንሻል ነውና መሐሪ።

አምላክ ሆይ አድነን አውጣን ከፈተና
ሕግህን ተላልፈን በድለናልና።

ባደረገቺው ግፍ በሠራቺው ኃጢአት
ከእንግዲህ ፈርጀ ምድርን ላላጠፋት
ለቃል ኪዳን ማጽኛ ለውል ስምምነት
በእኛ መካከል ለእውነት ምልክት
ስየ አሳይሃለሁ ቀስቴን በደመና
ብለህ በነገርከው ለኖኅ በቅድምና
ፈጣሪሆይ ማረን መሐሪ ነህና።
ከፊቷ መትረየስ ከኋላዋ መድፍ
በስተቀኞ ታንክ በግራዋም ሰይፍ
ከበው ሲያስጨንቋት ኢትዮጵያን በሰልፍ
ፈርታ ተንቀጥቅጣ ደንግጣ ተዳክማ
ይኸው ታለቅሳለች መካከል ላይ ቆማ
እምዬ ኢትዮጵያ ባልቴቲቱ እማማ
ይኸው ታለቅሳለች መካከል ላይ ቆማ።

ስለ ዚህ ፈጣሪ ሳትጠፋ ፈጽማ
ፈጥነህ ታወጣት ዘንድ ከጥፋት አውድማ
ልቅሶዋን አዳምጥ ጩኸቷንም ስማ።

ለአብርሃም ለይስሐቅ ለያዕቆብ ብለህ
የማልክላቸውን ለጥንት ወዳጆችህ
ፈጣሪ ሆይ አስብ ጎብኘን በምህረትህ
አቤቱ አታጥፋን በደላችን ቆጥረህ።

ወንጌልን ለዓለም ዞረው ባበሠሩ
በማያምኑትም ፊት ሳይፈሩ ሳያፍሩ
ስምህን በይፋ ቆመው ባበሠሩ
 በሐዋርያትህ ስም ማረን አንተ ቸሩ።

ኃጢአታችን በዝቶ ዕውን ቢሆን ዛሬ
ምድር ተለውጣ ሆነቺብን አውሬ።

በክፉ አሟሟት በከንቱ እንዳናልቅ
አቤቱ አምላካችን ፍጥረትህን ጠብቅ።

ማረን እራራልን አንተ አምላከ ሰላም
ልትከዳን ነውና ይህች የተውሶ ዓለም።

ወዳንተ እንጮሃለን በልቅሶ በዋይታ
የምሕረት ባለቤት ማረን አንተ ጌታ
አምላከ አብርሃም ወአምላከ ሣራ
አምላከ ኤልያስ ወአምላከ ዕዝራ
ኢትዮጵያን አደራ ኢትዮጵያን አደራ
እንለምንሃለን ልጆቿ በጋራ።

 ይህ ግጥም “የጸጋ ግምጃ ቤት” ከተሰየው የግጥም መድበል መጽሐፌ ተወስዶ መጠነኛ ለውጭ ተደርጎበታል ።
መጽሐፉን ለመግዛት የሚከተለውን ይጫኑ(ራሱ መጽሐፉን ይጫኑ።
 

Monday, June 24, 2019

የጭንቅ ሰቆቃ ሥነ ግጥም/Yechink Sekoka poem by Mhr Melaku




የጭንቅ ሰቆቃ ስነ ግጥም ስለ አገራችን ወቅታዊ ሁኔታዎች 
ግጥሙ ያለበትን መጽሐፍ ለመግዛት ይህንን ሊንክ ይጫኑ

https://amzn.to/2Rvwu5I

Sunday, June 16, 2019

ቃለ - መጠይቅ ከመጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ጋር/Interview with Megabe Hadis Eshetu Alema...




መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህር፤ እንዲሁም የመጻሕፍት
ትርጓሜና የቅኔ መምህር እና መም/ር መላኩ አስማማው የአውደ ጥናት እና የአውደ ጥናት ዘግእዝ መሥራችና አስተማሪ ቃለ - መጠይቅ ከመጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ጋር/Interview with Megabe Hadis Eshetu Alemayehu

ስለ ግእዝ ቋንቋ ቅድመ ታሪክ፤ ይዘትና ጥቅም፤ እንዲሁም ስለ አውደ ጥናት ዘግእዝ የትምህር አሰጣጥ ዘዴ ሰፋ ያለ ማብራርያ ይሰጣሉ ፤ ለሌሎችም ሸር ያድርጉ

ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን የተባለውን መጽሐፍ ለመግዛት የሚከተለውን ይጫኑ

Saturday, June 15, 2019

“For US and For Them” ለኛም ለነሱም


“For US and For Them” ለኛም ለነሱም 






“ለኛም ለነሱም” 
ለኛም ለነሱም :- 
ማለት እኛ እንግሊዘኛ የምንማርበት፤
 እነሱም አማርኛ የሚማሩበት ማለት ነው።

“ለኛም ለነሱም በተሰኘው”
በዚህ ርእስ መሠረታዊ መግባቢያ
የሚሆን የአማርኛ ቋንቋ 

ለውጭ ዜጎችና በውጭ ለተወለዱ
ኢትዮጵያውያን የሚሰጥ ሲሆን እንዲሁም 

መሠረታዊ የሆነ
የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርትን
 መማር ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን
የእንግሊዘኛ ትምህርት ይሰጥበታል።
 በመሆኑም “በአንድ ወንጭፍ
ሁለት ወፍ”እንደ ማለት ነው።
 (በመልካም መንገድ ሲተረጎም)
 ወይም “ሰይፍ ዘክልኤ አፉሁ”
ማለት ሰይፍ በሁለቱም ጎን በኩል
 ስለት ያለው ነው ማለት በሁለቱም
 የሚሠራ ለማለት ነው።ስለዚህ
ይህም ድረ-ገጽ ሁለት የተለያዩ ቋንቋዎችን
በአንድ ጊዜ ያስተምራል ማለት ነው።

Teaching Amharic Language
 for Amharic and non-Amharic
speakers as well
as Teaching Basic English
 for Amharic speakers
















ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን የተሰኘውን
 ይህንን መጽሐፍ እና ሌሎችንም 
መጻሕፍቶቼን ከአማዞን ለመግዛት 
የሚከተለውን(መጽሐፉን) ይጫኑ።






English letters/ የእንግሊዘኛ ፊደላት
  For Us/ ለኛ

6ቱ የእንግሊዘኛ ፊደላት ሲሆኑ 5ቱ 
በቀይ የተከበቡት አናባቢዎች፤ "ዋይ" 
የተባለውና በቀይና በቡናማ ቀለም
የተከበበው ሆሄ  ግማሽ አናባቢ
(አንዳንድ ጊዜ አናባቢ
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ተናባቢ)
ሲሆን ቀሪዎቹ  ማለትም
ሃያዎቹ ሆሄያት ደግሞ ተናባቢዎች ናቸው። 
 ማለትም፡ A, E, I, O, U
ሙሉ በሙሉ አናባቢዎች ሲሆኑ "Y" 
ተባለው ሆሄ ግን  አልፎ አልፎ
አናባቢ በመሆን ይሠራል።
ይህ ማለት የእንግሊዘኛ
ፊደላት ትርጉም ሊኖራቸው የሚችለው
አናባቢና ተናባቢ ተቀላቅለው ሲጻፉ ነው። 


















ከዚህ በላይ ያሉትን
 አናባቢዎችና ተናባቢዎች 
ለይታችሁ እወቁ ማለትም
 የያንዳንዱን ፊደል ስም ጻፉ፤
 እንዲሁም  ስንት ትናባቢ ፊደላት አሉ?
ስንት አናባቢ ፊደላት አሉ?
ስንት አናባቢም ተናባቢም ፊደላት አሉ?  
የሁሉም የእንግሊዘኛ ሆሄያት
ድምራቸው ስንት ነው?  
ለአምስቱም ጥያቄዎች መልስ ስጡ


ከዚህ በላይ ባሉት ሁለት 
የእንግሊዘኛ ቃላት  
የእንግሊዘኛ አናባቢዎች
(Vowels) ሁሉ አሉባቸው 
ስለዚህ አናባቢዎቹን 
ለይታችሁ በማውጣት 
ለብቻቸው ጻፉ።



ከዚህ በታች ያሉት ደግሞ
ፊደላቱ በትልቅ እና በትንሽ

(ካፒታል ሌተር እና 
ስሞል ሌተር) ሲጻፉ ነው/ 

Capital or 
small letters

(also called upper
and Lower case)


















For Them/ለነሱ
Comparing Amharic letters

 with English Learn 
the Amharic Alphabet





For Example: 
This letter “ሀ” is Called Ha (He)
  and has the sound of  “H” 
 so, it replaces
 the English letter “H” and
has 7 branches
with similar sounds  
and they replace the vowels.
1.     = He
2.    = Hu
3.    = Hi
4.    = Ha
5.    = Hia
6.    = H
7.    = Ho 

Self-Introducing/
ራስን ማስተዋወቅ
For Us/ለኛ:


ይህንን ድረ-ገጽ የጀመርኩት
ለውጪው ዓለም
 አዲስ የሆኑ ወገኖች
ሊኖሩ ስለሚችሉ
በመጠኑም ቢሆን
መሠረታዊ የእንግሊዘኛ
ቋንቋን ለማጥናትና
በሥራ ቦታም ሆነ
በትምህርት ቤት
በቀላሉ ለመግባባት
ያስችላቸዋል
ብየ በማሰብ ነው።


Hello, my name is 
Melaku; I am from Ethiopia.= 
ሰላም ስሜ መላኩ ይባላል(ነው) 
እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ.

For Them/ለነሱ:

 Selam, Smie Melaku
Yibalal (naw)

Giving Personal Information= 
ስለ ራስ ማንነት መናገር
ወይም ማስተዋወቅ የቃላት ትርጉሞች፤ 

Giving = መስጠት፤ 
Personal = የግል 
Information =መረጃ 


ከዚህ በታች ባሉት 
ቃላት መሠረት ራሳችንን
 ስናስተዋውቅና ሌላውን ስንጠይቅ 

My name is ----
I came from----
What is your name?


Where are you from?
የቃላት ትርጉም
my = የኔ
name=ስም
is= ነው/ናት
My name is ----=
ስሜ/የኔ ስም ----ነው 
(በባዶ ቦታው ላይ 

ስማችንን ማስገባት ነው)

ለምሳሌ፡ እኔ 
My name is Melaku
ብል "ስሜ ወይም
 የኔ ስም መላኩ ይባላል 
ማለት እችላለሁ። እናንተም 
እንደዚሁ ስማችሁን ማስገባት 
ትችላላችሁ።

የቃላት ትርጉም
I = እኔ
Came= መጣሁ፤መጣ፤ 
መጣች፤ መጡ፤ 
መጣን ወዘተ ማለት ነው

From = ከ
I Came from---= እኔ
 ከ----መጣሁ (የመጣሁት) 
ከ---ነው (በባዶ ቦታው ላይ
የመጣንበትን ቦታ/

አገር መናገር ነው) 
ለምሳሌ እኔ እንደሚከተለው
ማለት እችላለሁ።
I came from Ethiopia.

የቃላት ትርጉም
What = ምን
Your name =
ስምህ (ያንተ ስም)
what is your name?=
ስምህ ማነው (ምንድነው፤
 ወይም ማን ይባላል) 

ለምሳሌ What is your name?
 ተብየ ብጠየቅ 


My name is Melaku
በማለት መልስ መስጠት እችላለሁ ።
 ስሜ መላኩ ነው/ ወይም መላኩ

እባላለሁ ወይም ስሜ መላኩ
 ይባላል ማለቴ ነው።

የቃላት ትርጉም

Where= የት/ከየት?

are= ነን፤ናቸው፤ናችሁ

Where are you from?= 
ከየት አገር ነህ/የት ነው አገርህ?

Wher are you from? 

ተብየ ብጠየቅ

"I am from Ethiopia"
 በማለት እመልሳለሁ 

"ከኢትዮጵያ ወገን ነኝ
ወይም ኢትዮጵያዊ ነኝ/

ከኢትዮጵያ ነኝ 
ወዘተ ማለት ነው።







በአማርኛ መሪዎች ወይም
የስም ተለዋጮች እየተባሉ 
ይጠራሉ  ቁጥራቸው
 ስምንት ሲሆኑ
ከግእዝ በ2 ያንሳሉ።
እነሱም
እኔ

እኛ

አንተ

አንቺ
እናንተ
(ወንዶችም፤ሴቶችም)

እሱ

እሷ

እነሱ(ወንዶችም ሴቶችም)
በእንግሊዘኛ ፐርሰናል
ፕሮናውንስ ይባላሉ
ቁጥራቸው 6 ሲሆንከግእዝ
በ4 ከአማርኛ ደግሞ
በ2 ያንሳሉ።
ስማቸውም 
Personal pronouns

We

You (4)

He (it)

She (it)

They

አገልግሎታቸው የአንድን አካል፤
ወይም ነገር ስም ወክለው

ወይም ተክተው መሥራት
ወይም የዐ/ነገር ባለቤት
መሆን ነው።

አንደኛ ምሣሌ፡
መላኩ፡ ብለን በስም መጥራት
 ካልፈለግን

በስም ተለዋጭ ተክተን
 እሱ በማለት እንጠራዋለን

ስለዚህ መላኩ መጣ
በማለት ፈንታ
 “እሱ መጣ” እንላለን።

በመሆኑም“እሱ”
የሚለው“መላኩን”

ተካ ወይም የመላኩን
ድርሻ ያዘ ማለት ነው።

ለዚህም ነው
“የስም ተለዋጭ” የሚባለው።

ሁለተኛ ምሳሌ

“አልማዝ” ብለን በስሟ መጥራት
 ካልፈለግን“እሷ”
 በማለት እንጠራታለን።
 ስለዚህ“
አልማዝ መጣች”
በማለት ፈንታ
“እሷ መጣች” እንላለን።

ሦስተኛ ምሳሌ፡
“መላኩና አልማዝ”
ብለን በስማቸው
 መጥራት ካልፈለግን

“እነሱ” እንላለን።
 ስለዚህ “አልማዝና መላኩ መጡ”

በማለት ፈንታ “እነሱ መጡ”
 እንላለን ማለት ነው።

ተውላጠ ስሞች/
 Personal Pronouns
 እና የአማርኛ ትርጉማቸው

· I = እኔ

· We = እኛ

· You = አንተ

· You = አንቺ

· You = እናንተ

· You = እናንተ

· He = እሱ

· She = እሷ

· It = እሱ
(ለእቃ፤ ለማይሰማ ነገር)

· They = እነሱ
በሚከተለው መልኩ
ዐ/ነገር ይሠራባቸዋል

· I am = እኔ ነኝ

· We are = እኛ ነን

· You are = አንተ ነህ

· You are = አንቺ ነሽ

· You are = እናንተ ናችሁ

· You are = እናንተ ናችሁ

· He is = እሱ ነው

· She is = እሷ ናት

· They are = እነሱ ናቸው

· They are =
 እነሱ ናቸው
ባለቤትነትን
የሚያመለክቱ ቃላት
/Possessive Pronouns =

ባለቤትነትን የሚያመለክቱ ቃላት
ከዚህ በታች ያሉት ቃላት
ሁለት ሁለት ናቸው
ሁለቱ ባለቤትነትን
የሚያመለክቱ ናቸው
ላሁኑ ሁለቱም
አንድ ዓይነት ትርጉም አላቸው
በሚቀጥለው ትምህርት

ሁለቱን ማለትም
 የያንዳንዳቸውን
 ልዩነት እናያለን።

ላሁኑ አንድ ምሳሌ እንሆ :
ከጽሁፉ መጨረሻ ላይ

አንድ መጽሐፍ አለ
 ይህ መጽሐፍ የማን
መሆኑን ለመግለጽ

አንድ አመልካችን እንጠቀም
 (የሷ መጽሐፍ ለማለት)*

1st person singular
 and plurals

Ø My = የኔ
 (need subject
or object)

Ø mine = የኔ

Ø የኔ

Ø -------------

2nd person singular
and plurals

Ø Our =

Ø ours =

Ø የኛ

Ø የኛ

Ø ----------

3rd person singular
 and plurals

Ø Your =

Ø yours =

Ø ያንተ፤

Ø የናንተ፤

Ø ያንቺ፤

Ø የናንተ

----------

Ø Their =

Ø theirs =

Ø የነሱ፤

Ø የነሱ

-----------

Ø His =

Ø It's =

Ø የሱ፤

Ø የሱ

----------

Ø Her =

Ø Hers

Ø የሷ፤

Ø የነሱ

Example/ምሳሌ፡
---Her book =

የሷ መጽሐፍ ማለታችን ነው፡

ላሁኑ ቃላቱን ብቻ አጥኑ

(ማለትም የተጻፈውን ትርጉም
 በቃል መያዝ ነው)

በሚቀጥለው በዐረፍተ ነገር

እያስገባን እንማራለን።







Thursday, June 13, 2019

እምነትሽ ያድንሽ-ግጥም/Let your faith saves you-poem



“… በልጅ የመደሰት ዕድሉም ከሌለሽ፣
ትካዜ ጩኸቱን ስሞታውን ትተሽ
ጸሎት አቅርቢና ወደ ቸሩ አምላክሽ
በልቡናሽ ያለው እምነትሽ ያድንሽ”

መጻሕፍቶቼን ለመግዛት የሚከተለውን ይጫኑ

Saturday, June 8, 2019

Megabe Hadis about the Orthodox Church song contents/ መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮች ይዘት

Megabe Hadis Eshetu Alemayehu teaches about what the Orthodox Church songs should includes/ መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮች ይዘት 

መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ የሰዋስወ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህር፤ የመጻሕፍት ትርጓሜና የቅኔ ምሁር  ናቸው 
መጋቤ ሐዲስ እሸቱ ስለ ቅዱስ ያሬድ መዝሙራት እና በአጠቃላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙራት ምን ምን መሠረታውያን ነጥቦችን በውስጣቸው ማካተት እንዳለባቸውና ከሌሎች ሃይማኖታዊ መዝሙራት መለየት እንደሚገባቸው ሰፋ አድርገው ይገልጻሉ። 
ቪዲዮውን ለመስማት ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ተጫኑ፤ ሌሎችንም ልዩ ልዩ ትምህርቶችን ለማግኘት ሰብስክራይብ አድርጉ፤ ሸርም አድርጉት። እግዚአብሔር ይባርከዎ።
ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን የሚለውን እና “ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ይተዋወቁ” የሚባለውን ሌሎችንም መጻሕፍት ለመግዛት የመጻሕፍቱን ሥዕል ይጫኑ
ሁለቱ  ተወዳጆቹ መጻሕፍቶቼ!!
እነዚህን መጻሕፍት ልታገኞቸው ይገባል፤ በውነትም ይረኩባቸዋል።


ስለ መጻሕፍቶ ማብራርያና ይዘት የሚከተለውን ያንቡ

ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ይተዋወቁ

የተሰኘው ይህ መጽሐፍ ሦስት ምዕራፎችንናአሥር አበይት ክፍሎችን የያዘ ሲሆንበመጽሐፍ ቅዱስ ዙሪያ በአማርኛ ቋንቋከተጻፉ መጻሕፍት ሁሉ ባቀራረቡና በይዘቱፍፁም የመጀመሪያው ነው ።

ስለመጽሐፍ ቅዱስና በመጽሐፍ ቅዱስውስጥ ስላለው ሁሉ በዚህ መጽሐፍ ተካቶይገኛል ። በቂ ግንዛቤ ከሌላቸው ጀማሪዎችእስከ መጽሐፍ ቅዱስ መምህራን ድረስከዚህ መጽሐፍ የማይለካ ዘርፈ-ብዙእውቀትን ያገኛሉ ይማሩበታል ያስተምሩበታልም ። ስለዚህ ስለእምነትዎ በሚገባ በማወቅም ሆነ በማሳወቅ ራሰዎን ፤ ቤተሰበዎንና ሕብረተሰቡን ሕያው

በሆነው በሕያው እግዚአብሔር ቃል ማነጽ ከፈለጉ ፤ ስለ እያንዳንዱ እምነት መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚል ፤የተለያዩ የሃይማኖትተቋማት የሚቀበሉት መጽሐፍ ቅዱስ እርሰዎ ከያዙት ጋር የሚመሳሰል ወይም የሚለያይ መሆኑን ማወቅ የሚሹ ከሆነ ፤ስለመጽሐፍ ቅዱስ የማስተማርና የመስበክ ሃላፊነት ካለብዎ ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማሪ ፤ ዲያቆን ፤ ቄስ ፤ መነኩሴ ፤ ጳጳስ ፤ኤጲስ ቆጶስ ወዘተ ከሆኑ፤ ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ዙሪያ ጥናት የሚያካሂዱ ከሆነ ፤ በአጠቃላይ ፍፁም የሆነውን

ሃይማኖታዊውንና ማኅበራዊውን ሕገ-መንግሥት ሊመሩበት ከወደዱ ፤ ከዘፍጥረት እስከ ራእየ-ዮሐንስ እንዲሁም 2ኛ የቀኖናመጻሕፍትን ጨምሮ በ81ዱ ፤ በ76ቱ ፤ በ73ቱ ፤በ66ቱና በ24ቱ የዕብራውያን ብሉይ ኪዳን የሚገኙ መጻሕፍት ሁሉ በቀላልና ልዩበሆነ ዘመናዊ አቀራረብ የመጽሐፉ ጸሐፊ ፤ የተጻፈበት ዘመንና ቦታ ፤ የመጽሐፉ ፍሬ-ሐሣብ ባጭሩ ፤ የመጽሐፉ ጠቅላላ ይዘትባጭር ትንታኔ፤

ምርጥ ጥቅሶች ፤ ልዩና ያልተለመዱ ፤ እንዲሁም የመጽሐፉ መልዕክት በሚሉ መሠረታውያን አርእስት የያንዳንዱ መጽሐፍ ይዘትማራኪ በሆነ መንገድ የመጽሐፉን ጠቅላላ ሐሣብ ባጭሩ ተምሮ በሰፊው መረዳት በሚያስችል ዘዴ ቀርቧል ።

በእኔ እይታ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነ ሁሉ ከልጅ እስካዋቂ ይህንን መጽሐፍ ሊይዝ ይገባል እላለሁ ። በመሆኑም እርሰዎም ከመጽሐፍ ቅዱሰዎ ጋር ተዋውቀው ያስተዋውቁት እላለሁ

ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን 
ይህ መጽሐፍ በመሠረታዊነት የተዘጋጀው ቋንቋውን ምንም ለማያውቁ ጀማሪዎችና መጠነኛ ግንዛቤ ኖሯቸው ሰዋስዋዊ አካሄዱን ግን ለማያውቁ ሲሆን ከዚያም በላይ የእውቀት ደረጃ ላሉም ቢሆን በተለይ የአገባብ መዋቅሮችን በተመለከተ ሰፊ ግንዛቤን እንዲሰጥ ታስቦ ነው።  


መጽሐፉን ካህናት፤ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፤ በየአብያተ ክርስቲያናት ሕጻናትንና ወጣቶችን በመሰብሰብ የእምነትንና የሥነ ምግባርን ትምህርት የሚያስተምሩ መምህራን ለማስተማሪያነትም ሆነ የግል እውቀትን ለማዳበር እንዲሁም በማነኛውም የቋንቋ ጥናት ላይ የሚገኙ ተማሪዎች የቋንቋን አካሄድ፤ የቃላትን ቅንብርና አገባብ ለመገንዘብ ሊጠቀሙበት ይችላሉ። 


 መጽሐፉ ቀላልና ግልጽ በሆነ የአጻጻፍ ስልት ቢጻፍም “ያለ መምህር መማሪያ” ለመሆን ከበድ ሊል ይችላል ብየ አምናለሁ። በመሆኑም “አውደ ጥናትን መጎብኘት አይዘንጉ። 

ከዚህ መጽሐፍ ላቅ ያለ ዕውቀት ያላችሁ አንባብያን ለወጣንያንና ለማዕከላውያን1 የተዘጋጀ 1ኛ መጽሐፍ እንደ መሆኑ መጠንም በውስጡ የሚገኘው እያንዳንዱ ርእስ የተሰጠው ትርጉም፤ አገልግሎትና ትንታኔ ያለቀለት ሳይሆን ለክፍል አንድ የተመጠነ ብቻ ነው። ማለትም በክፍል ሁለትና በቀጣዮቹም ክፍሎች ትምህርቱ እየሰፋና እያደገ ወይም እየጨመረ የሚሄድ ነው። ስለዚህ አንድ ቃል ወይም አገባብ እናንተ የምታውቁትን ሁሉ አካቶ ባለመገኘቱ የተረሣ ወይም ሳይታወቅ የታለፈ እንዳይመስላችሁ፤ ለክፍል አንድ ተመጥኖ የቀረበ ስለሆነ ብቻ ነው።  


ሌላው ተማሪዎች ለጥናት የበለጠ እንዲተጉ በማሰብ በመጽሐፉ ውስጥ የቀረቡት ጥያቄዎች እየተመለስን መጽሐፉን እያነበብን የምንመልሳቸው ናቸው እንጅ መልሳቸው አልተሰጠም።