Saturday, June 8, 2019

Megabe Hadis about the Orthodox Church song contents/ መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮች ይዘት

Megabe Hadis Eshetu Alemayehu teaches about what the Orthodox Church songs should includes/ መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮች ይዘት 

መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ የሰዋስወ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህር፤ የመጻሕፍት ትርጓሜና የቅኔ ምሁር  ናቸው 
መጋቤ ሐዲስ እሸቱ ስለ ቅዱስ ያሬድ መዝሙራት እና በአጠቃላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙራት ምን ምን መሠረታውያን ነጥቦችን በውስጣቸው ማካተት እንዳለባቸውና ከሌሎች ሃይማኖታዊ መዝሙራት መለየት እንደሚገባቸው ሰፋ አድርገው ይገልጻሉ። 
ቪዲዮውን ለመስማት ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ተጫኑ፤ ሌሎችንም ልዩ ልዩ ትምህርቶችን ለማግኘት ሰብስክራይብ አድርጉ፤ ሸርም አድርጉት። እግዚአብሔር ይባርከዎ።
ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን የሚለውን እና “ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ይተዋወቁ” የሚባለውን ሌሎችንም መጻሕፍት ለመግዛት የመጻሕፍቱን ሥዕል ይጫኑ
ሁለቱ  ተወዳጆቹ መጻሕፍቶቼ!!
እነዚህን መጻሕፍት ልታገኞቸው ይገባል፤ በውነትም ይረኩባቸዋል።


ስለ መጻሕፍቶ ማብራርያና ይዘት የሚከተለውን ያንቡ

ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ይተዋወቁ

የተሰኘው ይህ መጽሐፍ ሦስት ምዕራፎችንናአሥር አበይት ክፍሎችን የያዘ ሲሆንበመጽሐፍ ቅዱስ ዙሪያ በአማርኛ ቋንቋከተጻፉ መጻሕፍት ሁሉ ባቀራረቡና በይዘቱፍፁም የመጀመሪያው ነው ።

ስለመጽሐፍ ቅዱስና በመጽሐፍ ቅዱስውስጥ ስላለው ሁሉ በዚህ መጽሐፍ ተካቶይገኛል ። በቂ ግንዛቤ ከሌላቸው ጀማሪዎችእስከ መጽሐፍ ቅዱስ መምህራን ድረስከዚህ መጽሐፍ የማይለካ ዘርፈ-ብዙእውቀትን ያገኛሉ ይማሩበታል ያስተምሩበታልም ። ስለዚህ ስለእምነትዎ በሚገባ በማወቅም ሆነ በማሳወቅ ራሰዎን ፤ ቤተሰበዎንና ሕብረተሰቡን ሕያው

በሆነው በሕያው እግዚአብሔር ቃል ማነጽ ከፈለጉ ፤ ስለ እያንዳንዱ እምነት መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚል ፤የተለያዩ የሃይማኖትተቋማት የሚቀበሉት መጽሐፍ ቅዱስ እርሰዎ ከያዙት ጋር የሚመሳሰል ወይም የሚለያይ መሆኑን ማወቅ የሚሹ ከሆነ ፤ስለመጽሐፍ ቅዱስ የማስተማርና የመስበክ ሃላፊነት ካለብዎ ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማሪ ፤ ዲያቆን ፤ ቄስ ፤ መነኩሴ ፤ ጳጳስ ፤ኤጲስ ቆጶስ ወዘተ ከሆኑ፤ ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ዙሪያ ጥናት የሚያካሂዱ ከሆነ ፤ በአጠቃላይ ፍፁም የሆነውን

ሃይማኖታዊውንና ማኅበራዊውን ሕገ-መንግሥት ሊመሩበት ከወደዱ ፤ ከዘፍጥረት እስከ ራእየ-ዮሐንስ እንዲሁም 2ኛ የቀኖናመጻሕፍትን ጨምሮ በ81ዱ ፤ በ76ቱ ፤ በ73ቱ ፤በ66ቱና በ24ቱ የዕብራውያን ብሉይ ኪዳን የሚገኙ መጻሕፍት ሁሉ በቀላልና ልዩበሆነ ዘመናዊ አቀራረብ የመጽሐፉ ጸሐፊ ፤ የተጻፈበት ዘመንና ቦታ ፤ የመጽሐፉ ፍሬ-ሐሣብ ባጭሩ ፤ የመጽሐፉ ጠቅላላ ይዘትባጭር ትንታኔ፤

ምርጥ ጥቅሶች ፤ ልዩና ያልተለመዱ ፤ እንዲሁም የመጽሐፉ መልዕክት በሚሉ መሠረታውያን አርእስት የያንዳንዱ መጽሐፍ ይዘትማራኪ በሆነ መንገድ የመጽሐፉን ጠቅላላ ሐሣብ ባጭሩ ተምሮ በሰፊው መረዳት በሚያስችል ዘዴ ቀርቧል ።

በእኔ እይታ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነ ሁሉ ከልጅ እስካዋቂ ይህንን መጽሐፍ ሊይዝ ይገባል እላለሁ ። በመሆኑም እርሰዎም ከመጽሐፍ ቅዱሰዎ ጋር ተዋውቀው ያስተዋውቁት እላለሁ

ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን 
ይህ መጽሐፍ በመሠረታዊነት የተዘጋጀው ቋንቋውን ምንም ለማያውቁ ጀማሪዎችና መጠነኛ ግንዛቤ ኖሯቸው ሰዋስዋዊ አካሄዱን ግን ለማያውቁ ሲሆን ከዚያም በላይ የእውቀት ደረጃ ላሉም ቢሆን በተለይ የአገባብ መዋቅሮችን በተመለከተ ሰፊ ግንዛቤን እንዲሰጥ ታስቦ ነው።  


መጽሐፉን ካህናት፤ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፤ በየአብያተ ክርስቲያናት ሕጻናትንና ወጣቶችን በመሰብሰብ የእምነትንና የሥነ ምግባርን ትምህርት የሚያስተምሩ መምህራን ለማስተማሪያነትም ሆነ የግል እውቀትን ለማዳበር እንዲሁም በማነኛውም የቋንቋ ጥናት ላይ የሚገኙ ተማሪዎች የቋንቋን አካሄድ፤ የቃላትን ቅንብርና አገባብ ለመገንዘብ ሊጠቀሙበት ይችላሉ። 


 መጽሐፉ ቀላልና ግልጽ በሆነ የአጻጻፍ ስልት ቢጻፍም “ያለ መምህር መማሪያ” ለመሆን ከበድ ሊል ይችላል ብየ አምናለሁ። በመሆኑም “አውደ ጥናትን መጎብኘት አይዘንጉ። 

ከዚህ መጽሐፍ ላቅ ያለ ዕውቀት ያላችሁ አንባብያን ለወጣንያንና ለማዕከላውያን1 የተዘጋጀ 1ኛ መጽሐፍ እንደ መሆኑ መጠንም በውስጡ የሚገኘው እያንዳንዱ ርእስ የተሰጠው ትርጉም፤ አገልግሎትና ትንታኔ ያለቀለት ሳይሆን ለክፍል አንድ የተመጠነ ብቻ ነው። ማለትም በክፍል ሁለትና በቀጣዮቹም ክፍሎች ትምህርቱ እየሰፋና እያደገ ወይም እየጨመረ የሚሄድ ነው። ስለዚህ አንድ ቃል ወይም አገባብ እናንተ የምታውቁትን ሁሉ አካቶ ባለመገኘቱ የተረሣ ወይም ሳይታወቅ የታለፈ እንዳይመስላችሁ፤ ለክፍል አንድ ተመጥኖ የቀረበ ስለሆነ ብቻ ነው።  


ሌላው ተማሪዎች ለጥናት የበለጠ እንዲተጉ በማሰብ በመጽሐፉ ውስጥ የቀረቡት ጥያቄዎች እየተመለስን መጽሐፉን እያነበብን የምንመልሳቸው ናቸው እንጅ መልሳቸው አልተሰጠም። 











No comments:

Post a Comment