Thursday, August 17, 2017

የእመቤታችን ስሞች

የእመቤታችን ስሞችና የአማርኛ ትርጉማቸው


ሰላም ጤና ይስጥልኝ ከአውደ ጥናት


“ሰላም ለክሙ አርድእተ ልሣነ ግእዝ ኵልክሙ ዮም እተረጉም ለክሙ ስማ አው አስማቲሃ ለእግዝእትነ ቅድስት ድንግል በክልኤ ማርያም”

በዛሬው ዝግጅታችን ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች በከፊል እንማራለን ። እንደሚታወቀው የተለያዩ የግእዝ ቃላትን ለማጥናት አልፎ አልፎ በማኅበራዊና በመንፈሳዊ ሕይወት ዙሪያ አርእስትን እየመረጥን እንደ ምንማር ተነጋግረናል፡ ባለፈው በማኅበራዊ ዙሪያ ስለ ተውኔትና ተዋንያን ተመልክተን ነበር ዛሬ ደግሞ በመንፈሳዊው ዙሪያ እንመለከታለን ማለት ነው። ስለ እመቤታችን ስሞች ዛሬ እንድንማር የመረጥኩበት ምክንያት።

1ኛ የእመቤታችን ስሞች ከግእዝ ቃላት በብዛት በሁለት ቃላት የተቀነባበሩና ተናባቢ ቃላትን ፤ የምን እና የማን የሚሉትን ባለቤትነትን የሚያመለክቱ ሆሄያትን የምናውቅባቸው  ናቸው ስለዚህ ቃላትን ልንማርባቸው ስለምንችል ነው
2ኛው በአሁኑ ወቅት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም መታሰቢያ ጾም የሆነው ጾመ ፍልሰታ ስለሆነ በረከትን የምናገኝበት በመሆኑ የእመቤታንን ስሞች መረጥኩ ማለት ነው።

እመቤታችን የምትጠራባቸው ስሞች በጣም ብዙዎች ስለሆኑ ሁሉንም ማጠቃለል ስለማይቻል የተወሰኑትን ማለትም ተዘውትረው የሚጠሩትን ብቻ ባጭሩ እንመለከታለን። ለወደፊቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በተመለከተ ሰፊና ተከታታይ ትምህርት ይኖረናል።

ስም የሚለው ቃል በግእዝም በአማርኛም አንድ ነው። ሲበዛ ግን አማርኛው፤ “ስሞች” ግእዙ ደግሞ “አስማት” ይሆናል። ስም የአንድ ነገር፤ አካል፤ ሁኔታ፤ ወዘተርፈ መጠሪያ ማለት ነው።

አብዛኛውን ጊዜ በተለይ በመጽሐፍ ቅዱስ በአገራችን ጭምር ስም እንዲሁ ለመጠሪያ ብቻ አይሰየምም፤ ነገር ግን ስም ሥራን፤ ባሕርይን፤ ዓይነትን፤ ሁኔታን፤ ክስተትን መሰረት በማድረግ ይሰየማል። በመሆኑም የእመቤታችንም ስሞች ማንነቷን፤ ሥራዋን፤ ምርጫዋን፤ ወዘተ መሠረት ያደረጉና የሚገልጡ ገላጮች ናቸው።

ስም ብቻውን ብዙ ነገገርን ይሠራል። ባለ ስሙ እንኳን በአካል ሳይኖር ብቻውን ብዙ ጥቅምን ይሰጣል። ለምሣሌ
“በእንተ ስማ ለማርያም” ወይም (ስለ እመ ብርሃን”) ማለት  “ስለ ማርያም ስም” ስለ ብርሃን እናት ስም ማለት ነው። “ስለ ማርያም ስም” ማለት ነው እንጂ ስሟ እንኳን በግልጽ አልተጠቀሰም። ነገር ግን  በዚህ ዐ/ነገር ብቻ አስደናቂ ሥራ ይሠራል። ምክንያቱም የእመቤታችን  ስም ተወዳጅ ፤ የሚፈራ፤ የሚከበር፤የሚናፈቅም ስም ስለ ሆነ ነው።

በዚህ ቃል ብቻ ሕይወታቸውን እየመሩ ነው የቤተ ክርስቲያናችን  ሊቃውንት ካህናት፤ የሀገርና የሕዝብ መመኪያዎች መምህራን፤ የአገራችንን ታሪክ ከምንጩ በብራና በእንስሳት ቆዳ በእጃቸው እየጻፉ ጥራቱን እንደ ጠበቀ ለትውልድ እንዲቆይ ያደረጉት። 

የዜማ፤የቅኔ፤የመጻሕፍት ትርጓሜ ሊቃውንት የሚማሩት በዚህ ስም ብቻ ነው። ይህንን ዐ/ነገር በመናገር ብቻ ነው። አስደናቂውንና ለወገን መመኪያ ከአምላክ ጋር መነናገሪያ መንፈሳዊ ቋንቋ የሆነውን መንፈሳዊ ትምህርት የተማሩት የእመቤታንን ስም በመጥራት ብቻ ነው። በተለይ በኢትዮጵያውያን መካከል የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ስም ልዩ ኃይል አለው። ማንም የእሷን ስም ጠርቶ ባዶ እጁን አይመለስም ። በገጠሩ ኅብረተ ሰብ ተማሪ “በእንተ ስማ ለማርያም” ካለ እንጀራ እንኳን ባይኖራቸው ለዘር ተብሎ ተደብቆ ከተቀመጠው እህል ቀንሰው ይሰጣሉ እንንጅ የለንም አይሉ። እና የእመቤታችን ስም ለተራቡት ምግብን፤ ለታረዙት ልብስን፤ ለተቸገሩት መጽናናትን ይሰጣል።

ከብዙ ዎቹ መካከል ከእመቤታችን ስሞች መካከል የሚከተሉት ጥቂቶቹ ናቸው እና እነዚህን በ2ቱ የጾመ ፍልሰታ ቀናት ምሣሌ 14ቱን ብቻ እንመለከታለን።

1.      ማርያም (ማር+ያም=) (ማ=ማኅደረ መለኮት፤ ር= ርግብ፤ ያ=ያንቅአዱ ኀቤኪ፤ ም= ምስአል ወምስጋድ፤)
2.     ድንግል (ቅጽል) (አምላክን ከመውለዷ በፊት፤ በወለደች ጊዜ፤ ከወለደችውም በኋላ) በሐሣቧ፤በሥራዋም ድንግል ናት
3.     ቅድስተ ቅዱሳን(ቀደሰ)(ቅጽል)
4.     እመ ብርሃን
5.     እመ አምላክ
6.     እመ ክርስቶስ
7.     ርኅርኅተ(ቅጽል) ልብ
8.     ሰአሊተ(ቅጽል) ምሕረት(ሰአለ)
9.     ጽንሰታ(ስም) ለማርያም (ጸንሰ)
10.    ልደታ(ስም) ለማርያም(ወለደ)
11.     በዓታ (ስም) ለማርያም(ቦአ)
12.    አስተርእዮታ(ንዑስ አንቀጽ)  ለማርያም(አስተርአየ)
13.    ፍልሰታ ለማርያም (ፍልሰተ ሥጋሃ ለማርያም
14.    ትንሣኤሃ(ስም/ጥሬ ዘር) ለማርያም(ተንሥአ)  ዕርገታ (ስም/ሳቢ ዘር) ለማርያም(አርገ)

ልዑል አምላክ ማስተዋሉን ያድለን

ከአውደ ጥናት ዘግእዝ


በመ/ር መላኩ አስማማው ቢሰጠኝ

Sunday, August 13, 2017

መልስ ለትርጉም ጥያቄዎች


መልስ
የትርጉም ጥያቄ  አንድ

ወደ አማርጛ ይቀይሩ


"ወሀሎ አሐዱ ብእሲ ዘስሙ መላኩ አስማማው ዘይነብር በብሔረ አሜሪካ ወውእቱ ይሜህር ልሳነ ግእዝ በውስተ አውደ ጥናት "

ትርጉም1፡ =
 በአሜሪካን አገር የሚኖር ስሙ መላኩ አስማማው የሚባል አንድ ሰው አለ፤ እሱም በአውደ ጥናት የግእዝ ቋንቋን ያስተምራል።

ወይም ትርጉም 2፡=
አንድ በአሜሪካን አገር የሚኖር ስሙ መላኩ አስማማው የሚባል አንድ ሰው አለ፤ እሱም የግእዝ ቋንቋን በአውደ ጥናት ውስጥ ያስተምራል (እያስተማረ ነው)።

የትርጉም ጥያቄ ሁለት

ወደ አማርኛ ይቀይሩ


“ዛቲ ጦማረ መልእክት ትብጻህ ኀበ አርድእተ ልሣነ ግእዝ ዘመጽሐፈ ገጽ
እምነ መምህረ ልሣነ ግእዝ”

ትርጉም አንድ፡=
ይህች የመልእክት ደብዳቤ በፌስ ቡክ የግእዝ ቋንቋ ተማሪዎች ወደ ሆኑት ትድረስ።
                      ከግእዝ ቋንቋ አስተማሪ(መምህር)
ወይም ትርጉም ሁለት፡=
ይች የሰላምታ ደብዳቤ ከግእዝ ቋንቋ  አስተማሪ(መምህር) በፌስ ቡክ የግእዝ ቋንቋን ወደ ሚማሩ ተማሪዎች ትድረስ።

የግእዝን ሥነ ጽሁፍ በተለያየ ዓይነት መልኩ በተለይ የቃላትን ቅደም ተከተል በመቀያየር ሊተረጎም ይችላል፤ ነገር ግን አንዳንድ መታለፍ የሌለባቸው ሕጎች አሉ።
ለምሣሌ

“ይሜህር ልሣነ ግእዝ ቢል”

1.      የግእዝን ቋንቋ ያስተምራል
2.     የግእዝ ቋንቋን ያስተምራል
3.     ግእዝን ያስተምራል


እነዚህ ሦስቱም ለሰሚ በትክክል ሊረዱ ይችላሉ ማለትም ተናጋሪው ምን ማለት እንደ ፈለገ ማወቅ ይቻላል። በሰዋስው ህግ ግን ትክክለኛው አፈታት ወይም ትርጉም ሁለተኛው(2ኛው ) ነው። ምክንያቱም “ን” የሚለውን ተሳቢ ወይም (Direct Object) ለማምጣት የቃሉ የመጨረሻ ሆሄ “ግእዝ” “ራብዕ” “ሐምስ” ወይም “ሣብዕ” መሆን አለበት ስለዚህ “የግእዝን ቋንቋ” ማለት አይቻልም ለምን “ግእዝ” የሚጨርሰው በ”ሳድስ” ልሣነ ግእዝ ሲል “ልሣነ” የሚለው በ”ግእዝ” ስለሚጨርስ ተሳቢ መሆን ይችላል።

ይህ አገላለጽ ለአሁኑ ሊከብዳችሁ ስለሚችል። ሌላ ጊዜ ስለ “ገቢርና ተገብሮ” ስንማር ቪዲዮ ስላለ በደንብ ይገባችኋል። አሁን ግን አትጨነቁ።


የተወሰናችሁት ሠርታችሁታል፤ በተለይ ትርጉሙን ምን ለማለት እንደተፈለገ በደንብ ሁላችሁም ታውቁታላችሁ። የሰጣችሁትም ትርጉም ለሁሉም ሰው ያለምንም ችግር ሊገባ ወይም ሊረዳ የሚችል ነው። ብቻ የቃላትን አገባብ ወይም ግራመር የሚያውቁ ሰዎች ብቻ ናቸው የሰዋስው ስህተት መኖሩን ሊያውቁ የሚችሉት።
እና በጣም ጥሩ እየተራመዳችሁ ነው በርቱ።

 የቤት ሥራ!!

አሁን የሚከተለውን ሥነ ጽሁፍ ማለትም የተረጎማችሁትን ወደ የራሳችሁ ወይም በራሳችሁ ስም ጻፉ(ቀይሩት) በሚከተለው ዓይነት ቃላቱ እንደየ ጾታችሁና የምትኖሩበት አገር ትቀይራላችሁ።

"ወሀሎ  አሐዱ  ብእሲ  ዘስሙ  መላኩ አስማማው     ዘይነብር  በብሔረ አሜሪካ   ወውእቱ ይሜህር ልሳነ ግእዝ በውስተ አውደ ጥናት ።"
----- ----- -----  -----         የራሳችሁን ስም           ----    የምትኖሩበት አገር    -----     -----    ልሣነ ግእዝ  ---     የምትኖሩበት አገር



ምን አልባት ቃላቱ እንዳይከብዳችሁ የሚከተሉትን ቃላት ተጠቀሙ።

ሀለወት =ለሴት አለች ወይም ነበረች
አሐቲ= ለሴት አንዲት
ብእሲት= ሴት
ዘስማ= ለሴት ስሟ
ዘትነብር= ለሴት የምትኖር
ወይእቲ= ለሴት እሷም
ትሜህር= ለሴት ታስተምራለች

ካልገባችሁ ከመሥራታችሁ በፊት ጠይቁ
መልካም ሥራ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
እምነ አውደ ጥናት ዘግእዝ


Wednesday, August 9, 2017

የግእዝ ቃላት ለቅማችሁ አውጡ/Find the Ge'ez words


የግእዝ ቃላትን  ለቅማችሁ አውጡ/Find the Ge'ez words 


“ፍልሰታ ለማርያም” በሚለው እና “የግል ጸሎት” በሚለው ቪድዮዎች ውስጥ የሚገኙትን የግእዝ ቃላት ለቅማችሁ አውጡ፤ ለሚለው ጥያቄ መልስ እንደሚከተለው ይሆናል። ምን አልባት ያልተጠቀሱ ተጠማሪ ቃላት ካሉ ንገሩኝ።





“የግል ጸሎት” በሚለው ቪዲዮ ውስጥ የሚገኙት የግእዝ ቃላት የሚከተሉት ናቸው። (የአማርኛ ትርጉማቸውን በስተቀኝ ባለው ሰንጠርጅ ተመልከቱ።

የግእዝ ቃላት
አማርኛ ትርጉማቸው
ማብራርያ
ስም
በቁሙ ስም(መጠሪያ)
በግእዝም በአማርኛም ስም ይባላል (በቁሙ ማለት አይቀየርም ማለት ነው)
ደቂቀ ሰላም
የሰላም ልጆች
ሰላም በቁሙ ሰላም ይባላል ትክክለኛው ግን መረጋጋት፤የመንፈስ ጸጥታ ማግኘት ወዘተ ማለት ነው
ሰላም
የመንፈስ/የውስጥ ጸጥታና መረጋጋት ተቃራኒው ብጥብጥ/ጸብ ወዘተ ነው

ፍቅር


አርድእተ ክርስቶስ
የክርስቶስ ደቀመዛሙርት/ተማሪዎች

አንትሙ
እናንተ ለወንዶች

ትግሁ
ትጉ (ለብዙ ወንዶች ለቅርቦቹ)

እስከ ይትፌጸም ተስፋሁ
ተስፋው እስከ ሚፈጸም

ሰላም ለክሙ
ሰላም ለናንተ ይሁን

በስመ አብ
በአብ ስም

እም አውደ ጥናት ዘግእዝ
ከግእዝ መማሪያ ከሆነችው ከአውደ ጥናት
አውድ አደባባይ/ መሰብሰቢያ ቦታ፤ ትምህርት መማርያ ወዘተ ይሆናል፤ ጥናት አማርኛ ነው
አብ
አባት
ከሦስቱ አካላት አንዱ እግዚአብሔር አብ
ወወልድ
በወልድም ስም

ወልድ
ልጅ
ከሦስት አካላት አንዱ እግዚአብሔር ወልድ
ወመንፈስ ቅዱስ
በመንፈስ ቅዱስም ስም

መንፈስ
ረቂቅ የማይጨበጥ የማይዳሰስ(የቃሉ ትርጉም ብቻ)
ከሦስቱ አካላት አንዱ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ
ም (ደቂቅ አገባብ)

ቅድመ ዓለም
ከዓለም በፊት

ማዕከለ ዓለም
በዓለም መካከል

ቅድም
መጀመሪያ/በፊት

ዓለም
ፍጥረት

ቅዱስ
ንጹህ፤ልዩ

ቅዱሳን
ቅዱስ የሚለው ሲበዛ ቅዱሳን ይሆናል (ለወንዶች)

ቅድስተ ቅዱሳን
ንጹህ፤ልዩ፤ ከሆኑት ይልቅ የነጻች፤የተለየች፤የከበረች

ቅድስት
ቅዱስ ለወንድ ሲሆን ቅድስት ለሴት ነው

ጸጋ
ሥጦታ (ነጻ የሆነ ከአምላክ የሚሰጥ ስጦታ)

ፍቅር
መውደድ
በአማርኛም ፍቅር ይባላል ትክክለኛው አማርኛ ግን መውደድ ነው
ትእግሥት
መቻል
በአማርኛም ትእግሥት ይባላል ትክክለኛው አማርኛ ግን መቻል ነው
ሞተ ነፍስ
የነፍስ ሞት

ዘልዓለማዊ
የሁል ጊዜ/የዘላለም(የማያልፍ)

ኃጢአት
በደል/ወንጀል
በአማርኛም ኃጢአት ይባላል ግን ትክክለኛው አማርኛ ወንጀል ነው
ንስሐ
ጸጸት
በአማርኛም በቁሙ ንስሐ ይባላል ግን ትክክለኛው አማርኛ ጸጸት ነው





“ፍልሰታ ለማርያም ወላዲተ አምላክ” በሚለው ቪዲዮ ውስጥ የሚገኙ የግእዝ ቃላት
የግል ጸሎት በሚለው ውስጥ የተጠቀሱትን ቃላት ድጋሚ ትርጉማቸውን ማስቀመጥ ስለማያስፈልግ አልፋቸዋለሁ።

የግእዝ ቃላት
አማርኛ ትርጉማቸው
ማብራርያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ


እግዚአብሔር (እግዚእ፤ አብ፤ ብሔር) ወይም “እግዚእ ብሔር
እግዚእ ጌታ፤ አብ አባት፤ብሔር አገር፤ ወይም ፍጥረት

ፈጣሪ
በቁሙ መፍጠር ከዜሮ ተነስቶ መፍጠር
ፈጣሪ የሚባለው እግዚአብሔር ብቻ ነው
ፍጡር
የተፈጠረ የተሰራ
በእግዚአብሔር የተፈጠረው ሁሉ ከእግዚአብሔር በስተቀር ሁሉም ፍጡር ይባላል
እምነት
በቁሙ ማመን

ጾም
በታቀብ፤ዝም ማለት፤ ከምግብ መከልከል

ትንሣኤ
መነሣት

እርገት
ወደላይ መውጣት

ትንሣኤሃ
መነሣቷ

እርገታ
ማረጓ ወይም ወደላይ መውጣቷ

ፍልሰታ
መፍለሷ/ከቦታ ቦታ መዘዋወሯ

ፍልሰት
መሰደድ/ከቦታ ቦታ መዘዋወር

ፈለሰ
ተሰደደ (ግሥ)

ፍልሰታ ለማርያም
የማርያም ከቦታ ቦታ መሰደድ (የቅዱስ ሥጋዋ ዝውውር)

ቅድስት


ቅድመ ክርስቶስ
ከክርስቶስ በፊት(ዘመነ ፍዳ)

ዓመተ ምሕረት
የምሕረት ዘመን/ዓመት(ዘመነ ይቅርታ)

ብሔረ ሕያዋን
የሕያዋን(ያልሞቱ ፍጡራን ወይም ሰዎች) አገር

ብሔር
ሐገር/ቦታ

ሕያዋን
ያልሞቱ (በሞተ ሥጋ ያልተለዩ)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይገባል

ስብሐት
ምስጋና

ተግሣጽ
ምክር

ቅድስና
ከፍ ከፍ ማለት/ልዩ ንፁህ መሆን

ራብዕ
አራተኛ

ድንግል
ጥብቅ/እንደ ተፈጠረች ወይም እንደ ተፈጠረ ያለ

ወላዲተ አምላክ
የአምላክ እናት/ወላጅ/የወለደች

ወላዲት
የወለደች

አምላክ
እግዚአብሔር/ፈጣሪ

ቅድስተ ቅዱሳን



ከአውደ ጥናት ዘግእዝ

በመም/ር መላኩ አስማማው