Thursday, February 26, 2015

ግእዝ ክፍል 22


የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ክፍል 22

ሰላም ለክሙ
አኃውየ ወአኃትየ
እለ ትነብሩ በውስተ ሐገሪትነ ኢትዮጵያ ወበውስተ ኵሉ ዓለም እፎ ኀለውክሙ? ወእፎ ኃለዉ አዝማዲክሙ? ወደቂቅክሙ?
ሰላመ እግዚአብሔር የሀሉ ምስሌክሙ ወምስለ ኵልነ።
በአገራቺን በኢትዮጵያና በመላው ዓለም የምትኖሩ ወንድሞቼና እኅቶቼ ሁላችሁ ሰላም ለናንተ ይሁን።
 ልጆቻችሁና ዘመዶቻችሁስ እንዴት ናቸው?
የእግዚአብሔር ሰላም ከእናንተና ከእኛ ጋርም ይሁን ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን

የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ክፍል 22
የሰላምታ ቃላት በግእዝ ቋንቋ
በዛሬው በክፍል 22 የግእዝ ትምህርታችን  ስለ ሰላምታ ልውውጥ እንማራለን።
ሰላምታ ሲባል
ሰዎች ሲገናኙ የሚለዋወጡት ሰላምታ፤ የሚሰጣጡት መልካም ምኞት ማለት ነው?
የሚከተሉት ቃላት በግእዝ ቋንቋ ለሰላምታ ከምንጠቀምባቸው ቃላት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
እነዚህም ሰላም፤ እፎ፤ ዳኅን  የሚሉት ሦቱ ቃላት ናቸው።
·         ሰላም= ማለት ጸጥታ/ የኅሊና ነጻነት፤ መረጋጋት/ ከረብሻና ከብጥብጥ ነጻ የሆነ ሕይወት ወዘተ ማለት ነው። ይህም የደስታ ምንጭ ነው ። ስለዚህ ሰላም ስንል ወይም ይህንን ቃል ለሌሎች ስናስተላልፍ
 = ሰላም ለአንተ ይሁን/ ለአንተ ሰላምታ ይገባል። ወይም  እንደ ምን አደርክ? እንደምን ዋልክ? እንደምን አረፈድክ? እንደምን አመሸህ? ማለታችን ነው።
·         እፎ= እንዴት/ እንደምን ማለት ሲሆን ለጥያቄ የሚያገለግል ነው።
·         ዳኅን= ደህና/ ጤና፤ሰላም ወዘተ ማለት ነው። “ኑ” የሚለውን ሆሄ በመጨመር እንደ መጠየቂያ ቃላት ያገለግላል።
ሰላም! ስንል = ወይም “ሰላም” በምንል ጊዜ  የሚከተሉትን ማለታችን ነው
·         ሰላም ለአንተ ይሁን/ለአንተ ሰላምታ ይገባል
·         እንደ ምን አደርክ/አረፈድክ/ዋልክ/አመሸህ? ለማለት ነው።

·       አሁን በግእዝ አጠቃቀማቸውን እንመልከት

ሰላም፡
ሰላም! = ሰላም ለአንተ ይሁን/ለአንተ ሰላምታ ይገባል (በአሥሩም መራህያን ሁሉ አስገባ)
ሰላም ለከ!= ሰላም ላንተ ይሁን

ሰላም እኁየ!= ሰላም ላንተ ይሁን ወንድሜ!
ሰላም ለከ እኁየ= ሰላም ላንተ ይሁን ወንድሜ

እፎ
         እፎ ሐደርከ? እኁየ?= እንዴት/ እንደምን አደርክ ወንድሜ ?
·         ሐደርከ
·         ጸናሕከ
·         ወአልከ
·         መሰይከ
·         ሀሎከ

ዳኅን፡ (በአሥሩ መራኅያን ተውላጠ ስሞች ሲገባ)

1.      ዳኅንኑ  አነ ? = እኔ ደኅና ነኝን? (ደኅና ነኝን?)

2.     ዳኅንኑ ንኅነ ? = እኛ ደኅና ነን? (ደኅና ነንን?)

3.     ዳኅንኑ ውእቱ ?= እሱ ደኅና ነውን? (ደኅና ነውን)

4.     ዳኅንኑ ውእቶሙ ?=እነሱ ደኅና ናቸውን(ደኅና ናቸውን?) ለወንዶች

5.     ዳኅንኑ ይእቲ ?= እሷ ደኅና ናትን?

6.     ዳኅንኑ ውእቶን ?= እነሱ ደኅና ናቸውን? (ለሴቶች)

7.     ዳኅንኑ አንተ ?= አንተ ደኅና ነኅን?(ደኅና ነኅን?)

8.     ዳኅንኑ አንትሙ ?= እናንተ ደኅና ናችሁን? (ደኅና ናችሁን?)

9.     ዳኅንኑ አንቲ ?= አንቺ ደኅና ነሽን? (ደኅና ነሺን?)

10.    ዳኅንኑ አንትን ?= እናንተ ደኅና ናችሁን? (ደኅና ናችሁን)



ሰላምታ ክፍል 2(ክፍል 23)


1.      ለከ= ለአንተ
2.     ለክሙ= ለናንተ
3.     ለኪ= ለአንቺ
4.     ለክን= ለናንተ
5.     ለሊሁ= ለእርሱ
6.      ለሊሆሙ= ለነሱ
7.     ለሊሃ= ለርሷ
8.     ለሊሆን= ለነሱ
9.     ለልየ= ለእኔ
10.    ለሊነ= ለእኛ

ይህ ሲተረጎም ከቀጥታ ቃላቱ ለየት ያለ አባባል አለዉ።
ይህም ሰላም የሚለው ቃል  +ለ+ የተውላጠ ስም (ስም) አመልካች  (ዝርዝር) + ይኩን(ይሁን) በማለት ይጨመራል ወይም ይገባል ማለት ነው።

ሰላም+ ለ+ የተውላጠስም ወይም ስም አመልካች (ሊሃ)+ ይሁን (ሰላም ለ-ሊሃ= ሰላም ወይም ሰላምታ ለእርሷ ይገባል) ይገባል የሚለው ማሠሪያ ለሊሃ ከሚለው ቃል ውስጥ የሚፈጠር ሲሆን የቋንቋው ባሕርይ ነው።
ለምሳሌ ሙሉ ዐረፍተ ነገር በመሥራት እንመልከት።

“ሰላም ለኪ አውደ ጥናት” ማላት አውደ ጥናት፣ (አውደ ጥናት ሆይ ሰላምታ ለአንቺ ይገባል፤ ለአንቺ ይሁን፤ ወይም እንደ ምን አደርሽ? ወልሽ? አረፈድሽ? አመሸሽ? ተብሎ ይፈታል። በመሆኑም ለከ= ላንተ፤ ለኪ=ላንቺ፤ ለክሙ=ለናንተ(ወንዶች)፤ ለክን= ለናንተ (ሴቶች)፤ ወዘተ እያልን በአሥሩ መራህያን ሁሉ በማስገባት መጠቀም እንችላለን። ቀጥለን በ10 መራህያን ትንታኔውን እንመልከት።

በአሥሩ መራህያን ሁሉ እያስገባን የሰላምታ አይነቶችንና አተረጓጎማቸውን እንመልከት።
1.      አንተ = አንተ  በሚለው ተውላጠ ስም፡

ሰላም - ለከ= ሰላምታ ለአንተ ይገባል ( እንደ ምን ዋልክ? እንደምን አደርክ? አመሸህ/አረፈድክ ወዘተ ይሆናል)
2.     አንት= እናንተ

ሰላም - ለክሙ= ሰላም (ሰላምታ) ለናንተ ይገባል፤ ለናንተ ይሁን፤ (እንደ ምን አደራችሁ?)
3.     አንቲ= አንቺ

ሰላም - ለኪ= ሰላምታ ለአንቺ ይሁን (እንደ ምን አደርሽ)
4.     ንትን= እናንተ (ሴቶች)

ሰላም - ለክን= ሰላምታ ለእናንተ ይሁን (እንደ ምን አደራችሁ?)
5.     እቱ= እሱ

ሰላም - ለሊሁ= ሰላምታ ለሱ(ለእሱ)ይገባዋል ይገባል( እንዴት አድሯል? (በመልእክት)
6.     እቶሙ= እነሱ (ወንዶች)

ሰላም - ለሊሆሙ= ሰላምታ ለነሱ ይገባል ( እንደምን አሉ፤ ናቸው፤ አድረዋል፤ሰንብተዋል) ሰላም በሉልኝ
7.     እቲ= እሷ

ሰላም ለሊሃ= ሰላምታ ለ እርሷ ይገባል፤ ለ እርሷ ይሁን፤ (እንደ ምን አድራለች?)
8.     እቶን= እነሱ (ለሴቶች)

ሰላም ለሊሆን= ሰላምታ ለእነርሱ ይገባል፤ይሁን፤ እንደ ምን አሉ፤ ናቸው?
9.     አነ= እኔ (ለሴትም፤ ለወንድም)

ሰላም - ለልየ= ሰላምታ ለእኔ ይገባል(ይገባኛል)
10.    ንሕነ== እኛ (ለሴቶችም፤ ለወንዶችም)

ሰላም - ለሊነ= ሰላምታ ለ እኛ ይገባል።

Friday, February 6, 2015

ግእዝ ክፍል 21

የግእዝ ትምህርት ክፍል 21

መራኁት


መራኁት ማለት?
¨  መራኁት ማለት መክፈቻዎት ማለት ሲሆንመርኆየሚለው ቃል ብዜት ወይም ብዙ ቁጥር ነው
¨  መርኆ
¨  = መክፈቻ ማለት ነው
¨  መራኁት =
መክፈቻዎች ማለት ነው ለብዙ ቁጥ
መራኁት የሚባሉት ሆሄያት ሲሆኑ 5 ናቸው
¨  ግእዝ፤ (መጀመሪያ ወይም 1)
¨   ራብዕ፤ (አራተኛ ወይም 4)
¨   ሐምስ፤ (አምስተኛ ወይም 5)
¨  ሳድስ፤ (ስድስተኛ ወይም 6)
¨  ሳብዕ፤ (ሰባተኛ ወይም 7)
ናቸው።
ዘርግስ 5 መራኁት ብቻ ይጀምራል
መራኁት በአምስቱ ሆሄያት ሲጀምሩ 
የሚያሳይ ምሳሌን በሚቀጥሉት 5
(አምስት) ገጾች ይመልከቱ
ዘር ግሥ በካዕብና በሳልስ አይነሣም
መራኁት በግእዝ ሆሄ ሲጀምሩ
¨  ሐለመ
¨  ከፈለ
¨   አእመረ
¨   ተንበለ
መራኁት በራብዕ ሆሄ ሲጀምሩ
¨  ባረከ
¨  ሣረረ
¨  ፃዕደወ
መራኁት በሐምስ ሲጀምሩ
¨  ሤመ
¨  ኄለ
¨  ዔለ
መራኁት በሳብዕ ሲጀምሩ
¨  ቆመ
¨  ሖረ
¨  ጾመ
¨  ሆከ
መራሁት የማይጀምሩባቸው
ወይም የማይነሡ ባቸው ሆሄያት
¨  ካዕብ (ሁለተኛ ሆሄ)
¨  ሳልስ (ሦስተኛ ሆሄ)
በነዚህ ሆሄያት ዘር ግሥ አይጀምርም
የቃላት ትርጉም
¨  ሐለመ=
¨   አለመ (ሕልም)
¨  ከፈለ=
¨  ከፈለ (መክፈል) አደለም ይሆናል (ዕድል)
¨   አእመረ=
¨   አወቀ
¨   ተንበለ=
¨   ለመነ፤ አማለደ
¨  ባረከ=
¨  ባረከ፤ መረቀ
¨  ሣረረ=
¨   መሠረተ፤ ተከለ፤ ሠራ
¨  ፃዕደወ =
¨   ነጣ(ነጭ)
¨  ሤመ=
¨  ሾመ
¨  ኄለ=
¨  ወጣ፤ እልል አለ፤ ደነፋ
¨  ዔለ=
¨   ዞረ
¨  ቆመ=
¨  ቆመ
¨  ሖረ=
¨   ሄደ
¨  ጾመ=
¨  ጾመ
¨  ሆከ=
¨  አወከ


Monday, February 2, 2015

ግእዝ ክፍል 20

Learn Ge'ez Language part 20 Sentences structures and vocabularies 


ንዋያተ ቅድሳት(ለብዙ)
ጻድቅ = እውነተኛ
ጻድቃን (ለብዙ)
ሰማዕት =ምስክር
ሰማእታት (ለብዙ)
ተሰጥዎ = መልስ፤ ስጦታም ይሆናል።
መዝሙር = ምስጋና   
ቁርባን = የሚቀበሉት፤ የሚያቀብሉት(ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ)
ጽንሰታ = መወለድ (መወለዷ)
ልደታ =መወለዷ
በዓታ = መግባቷ(መግባት)
ፍልሰታ =መሰደድ፤መዛወር
ንስሐ =ጸጸት
ተዝካር = መታሰቢያ
ዝክር =መታሰቢያ
ምግባር = ሥራ
ኃጢአት = ወንጀል
ክህነት =አገልግሎት
ካህን=አገልጋይ
ዲያቆን=ተላላኪ(ለመንፈሳዊ አገልግሎት)
ክርስቲያን= ክርስቶሳዊ
ኦርቶዶክስ=ቀጥተኛ ምስጋና (አምልኮት) (ግሪክ)
ተዋሕዶ= ያለመቀላቀል፤ያለመለያየት፤ያለመጠፋፋት፤ ያለመለዋወጥ አንድ መሆን
ሥጋዌ = ሰው መሆን
ትንሣኤ ሙታን = የሙታን መነሣት
መድኃኔ ዓለም =የዓለም መድኃኒት
በአለ ወልድ = የወልድ በአል፤ክብር
አብ =አባት
ወልድ=ልጅ
ልሳን=ቋንቋ
ወንጌል=የምሥራች
ሐዋርያት=ሐጅዎች የሚሄዱ
ነቢያት= ትንቢት ተናጋሪዎች
ደቀመዝሙር=ተማሪ
ጸሎት =ልመና (ወደ እግዚአብሔርና ወደ ቅዱሳን)
 ትእግሥት =መቻል
ወላዲተ አምላክ = አምላክን የወለደች
እመብርሃን = የብርሃን እናት
መንግሥተ ሰማይ = የሰማይ መንግሥት
መልአክ = ተላላኪ፤አለቃ፤አስተዳዳሪ






የዐረፍተ ነገር ወይም የአገላለጽ እድገት ይህ ልምምድ ግእዝን ከማጥናት አልፎ
የሥነ ጽሁፍ ፍላጎት ላለው ሁሉ እጅግ ጠቃሚ ነው።

ከዚህ በታች የሚገኙትን የዐረፍተ ነገራቱን አቀማመጥ፤ ትርጉምና እንዴት ዐረፍተ ነገራቱ ሊስፋፉ ወይም ሊያድጉ እንደ ቻሉ ያስተውሉ። የራሰዎን ዐረፍተ ነገራት በመፍጠር ልምምድም ያድርጉ፡ በግእዝ ካቃተዎ በአማርኛ እየሠሩ ወደ ግእዝ ይቀይሩት።
1ኛ ምሳሌ
1.       መርድእ አእመረ= ተማሪ አወቀ
2.      መርድእ አእመረ ልሳነ =ተማሪ ቋንቋን አወቀ
3.      መርድአ ግእዝ አእመረ ልሳነ ግእዝ
=የግእዝ ተማሪ የግእዝ ቋንቋን አወቀ
4.      መርድአ ግእዝ አእመረ ልሳነ ግእዝ ተምሂሮ
=የግእዝ ተማሪ የግእዝ ቋንቋን ተምሮ አወቀ
5.      መርድአ ግእዝ አእመረ ልሳነ ግእዝ ተምሂሮ እምነ አውደ ጥናት
=የግእዝ ተማሪ የግእዝ ቋንቋን ከአውደ ጥናት ተምሮ አወቀ
6.     መርድአ ግእዝ አእመረ ልሳነ ግእዝ ተምሂሮ እምነ አውደ ጥናት ዘግእዝ
=የግእዝ ተማሪ የግእዝ ቋንቋን ማጥኛ ከሆነቺው ከአውደ ጥናት (ከግእዝ ትምህርት ቤት) የግእዝ ቋንቋን ተምሮ አወቀ
7.      መርድአ ግእዝ አእመረ ልሳነ ግእዝ ወ ቅኔ ተምሂሮ እምነ አውደ ጥናት ዘግእዝ
=የግእዝ ተማሪ የግእዝ ቋንቋን ማጥኛ ከሆነቺው ከአውደ ጥናት (ከግእዝ ትምህርት ቤት) የግእዝ ቋንቋን እና ቅኔን ተምሮ አወቀ

2ኛ ምሳሌ
የዐረፍተ ነገር ወይም የአገላለጽ እድገት ይህ ልምምድ ግእዝን ከማጥናት አልፎ የሥነ ጽሁፍ ፍላጎት ላለው ሁሉ
               እጅግ ጠቃሚ ነው።
·         መርድእ መጽአ
 =ተማሪ መጣ
·         መርድአ ቅኔ መጽአ
 = የቅኔ ተማሪ መጣ
·         መርድአ ቅኔ መጽአ እምነ ጎጃም
 = የቅኔ ተማሪ ከጎጃም መጣ
·         መርድአ ቅኔ መጽአ እምነ ጎጃም በእግሩ
= የቅኔ ተማሪ ከጎጃም በእግሩ መጣ
·         መርድአ ቅኔ መጽአ እምነ ጎጃም  እንዘ ይረውጽ በእግሩ
 = የቅኔ ተማሪ ከጎጃም በእግሩ እየሮጠ መጣ።


ከዚህ በላይ በ “1ኛ ምሳሌ” 1- 7 በተጠቀሱት ዐረፍተ ነገራት ውስጥ ለሚገኙት ቃላት ሙሉ ማብራርያ የያንዳንዱን ቃል ሙያ በአትኩሮት ይመልከቱ በ2ኛ ምሳሌ ሥር ያሉትም ከ1ኛ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይ ናቸው በቃላት ትርጉም ብቻ ነው የሚለያዩት ።

1 ባለቤትና ማሠሪያ  አለው( 2 አካላትን ይዟል) (Subject and Verb)
·         መርድእ = የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት (Subjet)
·         አእመረ = ማሠሪያ አንቀጽ(Verb)
2. ባለቤት፤ ማሠሪያ አንቀጽ፤ እና ተሳቢ (3 አካላትን ይዟል)( Subject; Verb, and Direct Object)
·         መርድእ = የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት (ዐረፍተ ነገሩ የሚነገርለት) ( Subject)
·         አእመረ = ማሠሪያ አንቀጽ(Verb)
·         ልሳነ = ተሳቢ (Direct Object)
3. ባለቤት፤ ማሠሪያ ቅንቀጽ፤ ዘርፍ፤ ተሳቢ፤የተሳቢ ዘርጅፍ (4 አካላትን ይዟል)
·         መርድአ = ባለቤት(Subjet)
·         ግእዝ = ዘርፍ (የመርድእ ዘርፍ ማለትም የባለቤቱ)
·         አእመረ = ማሠሪያ አንቀጽ(Verb)
·         ልሳነ = ተሳቢ ( የአእመረ ወይም የማሠሪያ አንቀጹ ተሳቢ)(Direct Object)
·         ግእዝ = የልሳነ ዘርፍ
4. ባለቤት፤ ማሰሪያ አንቀጽ፤ ዘርፍ፤ተሳቢ፤ ዘርፍ፤ ቦዝ አንቀጽ (6 አካላትን ይዟል)
·         መርድአ = የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት(Subjet)
·         ግእዝ = ዘርፍ ( የመርድ እዘርፍ)
·         አእመረ = ማሠሪያ አንቀጽ(Verb)
·         ልሳነ = ተሳቢ(Direct Object)
·         ግእዝ = የልሳን ዘርፍ
·         ተምሂሮ = ቦዝ አንቀጽ(የማያሥር)
5. ባለቤት፤ ማሠሪያ አንቀጽ፤ ዘርፍ፤ተሳቢ፤ ዘርፍ፤ቦዝ አንቀጽ፤ አገባብ(ከ)፤ አገባብ የወደቀበት፤ ዘርፍ፤ (8 ወይም 9 አካላትን ይዟል)
·         መርድአ = የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት(Subjet)
·         ግእዝ = ዘርፍ (የመርድእ ዘርፍ)
·         አእመረ = ማሠሪያ አንቀጽ(Verb)
·         ልሳነ = ተሳቢ(Direct Object)
·         ግእዝ = የልሳነ ዘርፍ
·         ተምሂሮ = ቦዝ አንቀጽ
·         እምነ = አገባብ ሲሆን ትርጉሙ “ከ” ማለት ነው
·         አውደ ጥናት = አገባብ የወደቀበት ማለትም እምነ ወይም ከ የወደቀበት
·         (ጥናት) = የአውድ ዘርፍ፤ “አውደ ጥናት” የሚለውን እንደ አንድ ስም ልንወስደውም እንቺላለን ግን ሁለት ቃላት ስለሆኑ ለያይቶ ማወቁ መልካም ነው።
6. ባለቤት፤ ዘርፍ፤አንቀጽ፤ተሳቢ፤ ዘርፍ፤ቦዝ አንቀጽ፤ አገባብ(ከ) አገባብ የወደቀበት፤ ዘርፍ፤አገባብ፤ የዘርፍ ዘርፍ (10 ወይም 11 አካላትን ይዟል)
·         መርድአ = ባለቤት(Subjet)
·         ግእዝ = ዘርፍ
·         አእመረ = ማሠሪያ(Verb)
·         ልሳነ = ተሳቢ(Direct Object)
·         ግእዝ = ዘርፍ
·         ተምሂሮ = ቦዝ አንቀጽ
·         እምነ= (አገባብ)
·         አውደ(ጥናት) = አገባብ የወደቀበት
·         ጥናት = ዘርፍ
·          ዘ = ትርጉሙ “የ” ማለት ሲሆን አገባብ ነው፤ ( የ”ዘ” ሥራ ብዙ ነው ለወደፊቱ ቀስ በቀስ እንማረዋለን ለአሁኑ ግን  “የ” የሚል ትርጉምን ብቻ ካወቅን ይበቃል።)
·         ግእዝ = አገባብ ያረፈበት ወይም የወደቀበት (ዘ ማለት ነው አገባብ ያልነው)

7. ባለቤት፤ ዘርፍ፤አንቀጽ፤ተሳቢ፤አጫፋሪ አገባብ፤ተሳቢ፤ ዘርፍ፤ቦዝ አንቀጽ፤ አገባብ(ከ) አገባብ የወደቀበት፤ ዘርፍ፤አገባብ፤ የዘርፍ ዘርፍ( 11 አካላትን ይዟል)
·         መድአ = ባለቤት(Subjet)                      
·         ግእዝ = ዘርፍ
·         አእመረ = ማሠሪያ (Verb)
·         ልሳነ = ተሳቢ(Direct Object)
·         ግእዝ = ዘርፍ
·         ወ = አገባብ ሲሆን አጫፋሪ ይባላል ሁለት ነገሮችን በአንድ ላይ ስለሚያያይዝ ነው
·         ቅኔ = ተሳቢ(Direct Object)
·         ተምሂሮ = ቦዝ አንቀጽ
·         እምነ =
·         አውደ (ጥናት) = አገባብ የወደቀበት
·         ጥናት = ዘርፍ
·         ዘ= (አገባብ)
·         ግእዝ = አገባብ የወደቀበት