Friday, December 19, 2014

ግእዝ ክፍል 19

Learn Geez Language Part 19/የግእዝ ትምህርት ክፍል 19

ባለፈው ትምህርታችን በክፍል 18 ማለት ነው የቅኔ ተማሪዎች በመምህራቸው የተዘረፈላቸውን ቅኔ እየመላለሱ ሲያጠኑ አይታችሁ ወይም ተመልክታችሁ ነበር ። በዛሬው በክፍል 19 ደግሞ መምህሩ የተቀኙትን ቅኔ ለተማሪዎቻቸው ሲፈቱላቸው ወይም ሲተረጉሙላቸው እንደምታዩና እኔም በትርጉሙ ላይ ባብራርያ እንደ ምሰጣችሁ ቃል ገብቼላችሁ ነበር ። ስለዚህ በገባሁት ቃል መሠረት ይዠላችሁ ቀርቤያለሁ ማለት ነው።
ዛሬ የምታዩት ቅኔ ጉባዔ ቃና ይባላል። የመጀመሪያው የቅኔ ክፍል ነው። ይህ የመጀመሪያ የሆነው የቅኔ ክፍል ሁለት ቤቶች አሉት ። ማለትም ቅኔ እንደሚታወቀው  የሚቀርበው በግጥም መልክ ሲሆን በሰምና  በወርቅ ወይም በሁለት ወይም ከሁለት በላይ በሆኑ ምሥጢራዊ ትርጉሞች የተቀነባበረ ነው። ይህ ማለት ተደራራቢ አባባል አለው ማለት ነው። ዛሬ የምናየው ሁለት ስንኝ ያለውን ቅኔ ወይም ግጥም ነው።ለዚህም ነው ሁለት ቤት ያለው ማለት ሁለት ስንኝ ያለው ማለት ነው።
 በአሁኑ ደረጃችን የምናተኩረው በቅኔው ሕግና በሰምና ወርቁ ላይ ሳይሆን የግእዝን ቋንቋ በማጥናቱ ላይ ነው ።
አንድ ተማሪ እያነበበ መምህሩ ደግሞ ትርጉሙንና ሰምና ወርቁን ሲያብራሩ፤ ጥያቄም እየጠየቁ ተማሪዎቹ ማለት ነው ሲከራከሩ ታያላችሁ እኔ የማነብላችሁም ያንኑ ቅኔ ነው ነገር ግን በደንብ ላይሰማችሁና ግልጽ ላይሆንላችሁ ስለሚችል የበለጠ ላስረዳችሁ ስለፈለግሁ ብቻ ነው። መልካም ትምህርት!


ጉባዔ  ቃና
1.    ኃያል ስምኦን ዘጽጌ ድንግል ጸገየ
2.     70 (ሰብአ) እደወ አምጣነ ገንጰለ ማየ። ይኸ ነው ቅኔው፤፡
በድንግል አበባ ያበበ የሆነ ስምኦን ኃይለኛ ነው
(ምክንያቱም) ሰባ ሰዎችን ወደውኃ ገልብጦ ጥሏልና (ገልብጧልና)
የእያንዳንዱ ቃል ትርጉምና የሥራ ድርሻ
ኃያል = ኃይለኛ ማለት ነው
 የስምኦን ቅጽል (ገላጭ) አድጀክቲብ ሆኖ 
ግን ውእቱ የቢባለውን አንቀጽ በውስጡ በማስገኘት
 የዐረፍተ ነገሩ ማሠሪያ አንቀጽ ሆኗል።
በዚህ ሙያው ( ኃያል ውእቱን መርምሮ ማሠሪያ ተብሎ ይጠራል)
ስምኦን = ስም ሲሆን ሙያው የዐረፍተ ነገሩ ወይም የቅኔው ባለቤት
= “የ” ማለት ሲሆን አገባብ  ሆኖ ጸገየ የሚለውን ግሥ እንዳያስር ይጠብቃል
ጸጌ = አበባ ማለት ነውስም ሲሆን “በ”  የሚል አገባብ የወጣበት ነው
ወይም “በ” ን ያስገኘ ነው ( አገባብ የወጣበት ይባላ)
ድንግል = የተፈጥሮ ለውጥ ያልታየባት ወይም ያልታየበት፤ ጥብቅ፤ እንደ ተፈተረ ያለ፤
 (በክብረ ንጽሕያ ያለ) ወዘተ ማለት ሲሆን የሥራ ድርሻው ወይም
 በዚህ አረፍተ ነገር ላይ ያለው ሙያ የጽጌ ዘርፍ ይባላል
 (ሁለት ቃላት ሲናበቡ መጨረሻ ላይ የሚገኘው ቃል ከኋላው ላለው ቃል ዘርፍ ይባላል።
ለምሳሌ ቤተ ክርስቲያን ስንል ክርስቲያን የሚለው ቃል የቤት ዘርፍ ይባላል።
ጸገየ  ግሥ ነው ነገር ግን በአንድ ቅኔ ላይ ሁለት ግሥ ማሰር ስለማይችል በ “ዘ”
 ተጠብቋል ወይ  አበበ አበባ አወጣ በማለት እንዳያሥር ተከልክሏል



70 = በቁሙ ቁጥር ነው ሙያው የእደው ቅጽል ነው
እደወ (እደው) = ወንዶች ማለት ሲሆን
ሙያው የገንጰለ ተሳቢ ነው ዳይሬክት ኦብጀክት ይባላል
አምጣነ = እና ወይን “ና” ማለት ሲሆን አብይ አበባብ ነው
ገንጰለ = ገለበጠ ማለት ሲሆን በሙያው እንዳያሥር አምጣነ ከልክሎታል።
 አምጣነ የውደቀበት ተብሎም ይጠራል (በዚህ ዐረፍተ ነገር ላይ)
ማየ (ማይ) = ውሀ ማለት ሲሆን “ወደ” የሚል አገባብን ያስገኘ ነው።
ስለዚህ አገባብ የወጣበት ይባላል።

No comments:

Post a Comment