Saturday, November 1, 2014

ግእዝ ክፍል 16 የ15 ማብራርያ

Part 16 Details for part 15 /ክፍል 16 ማብራርያ ለክፍል 15


የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ክፍል 16 ትርጉምና ማብራርያ ለግእዝ ቋንቋ ትምህርት ክፍል 15 ውይይት ወይም ጥያቄና መልስ በወይዘሮ ሶፍያና በአንድ ካህን መካከል።  ማስተዋሉን ያድለን።

ተስእሎት ወአውሥዖት/ጥያቀና መልስ /ውይይት

ለግእዝ ትምህርት ክፍል 15 ውይይት

ወ/ሮ ሶፍያ፡
እፎ ሐደርከ አቡየ?
አማርኛ፡
እንደ ምን አደርክ/አደሩ/አባቴ?
(እፎ የመጠየቂያ ቃል ነው “እንዴት እንደ ምን? ማለት ነው።) ሐደርከ፡ የሁለተኛ መደብ ተባ እታይ አንድ ወይም ነጠላ ግሥ ነው “አደርክ” ማለት ነው። “አቡየ” አባቴ ማለት ነው። “አብ” አባት ሲሆነ “የ” የእኔ ማለት ነው።
       

ካህን፡
እግዚአብሔር ይሰባህ እፎ ሐደርኪ ሶፍያ?
አማርኛ፡
እግዚአብሔር ይመስገን እንደ ምን አደርሽ ሶፍያ?
እግዚእ
አብ
ሔር
ይሰባህ ለሦስተኛ መደብ ተባእታይ ፆታ ነጠላ ግስ ነው።
ሐደርኪ፡ ለሁለተኛ መደብ አንስታይ ፆታ ነጠላ ግሥ ነው፡

ወ/ሮ ሶፍያ፡
እግዚአብሔር ይሰባህ። ባርከኒ አቡየ!

አማርኛ፡
እግዚአብሔር ይመስገን ባርከኝ አባቴ/ባርኩኝ አባቴ(በግእዝ ቋንቋ አንቱታ የለም)
ባርከኒ፡ የሁለተኛ መደብ ነጠላ ግሥ ለተባእታይ ፆታ ሲሆን ትእዛዝ አንቀጽ ይባላል።

ካህን፡
እግዚአብሔር ይባርኪ ወያብርህ ገጾ ላእሌኪ፡

አማርኛ፡
እግዚአብሔር ይባርክሽ ፊቱንም ያብራልሽ/ፊቱንም ወደአንቺ ይመልስ

ይባርኪ፡ ለሁለተኛ መደብ ለአንስታይ ፆታ ሲሆን ምርቃት ነው
ወ/ሮ ሶፍያ፡
ፍትሐኒ አቡየ! አስተስሪ ኃጢአትየ

አማርኛ፡
ይፍቱኝ አባቴ ኃጢአቴን አስተስርይልን/ይቅር በል

ካህን
እግዚአብሔር ይፍታህ/ ይፍታህኪ/እግዚአብሔር ያስተስሪ ለኪ ኃጢአተኪ

አማርኛ፡
እግዚአብሔር ይፍታሽ/ኃጢአትሽን ይቅር ይበል

ወ/ሮ ሶፍያ፡

አሜን፡ /ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ

አማርኛ፡
ይሁን ይደረግ/እንዳልከው ይህንልኝ

ካህን፡
እፎ ውእቶሙ(ሀለዉ) ደቂቅኪ ሶፍያ?

አማርኛ፡
ልጆችሽ እንዴት ናቸው ሶፍያ?

ወ/ሮ ሶፍያ፡
እግዚአብሔር ይሰባህ (ወውእቶሙ) ሰላመ ሐለዉ

አማርኛ፡
እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ናቸው/ደህና አሉ

ካህን፡
ሶፍያ, ለምንት ኢመጽኡ  (ደቂቅኪ) ኅበ ቤተ ክርስቲያን ምስሌኪ?

አማርኛ፡
ሶፍያ፣ ልጆችሽ ለምን ወደ ቤተ ክርስቲያን ካንቺ ጋር አልመጡም?

ወ/ሮ ሶፍያ፡
አቡየ, አነ ፈተውኩ ከመ አምጽኦሙ ምስሌየ አላ ኢክህሉ ከመ ይትነሥኡ እምነ ንዋሞሙ፡

አማርኛ፡
አባቴ፣ ልጆቼን ከእኔ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን እንዲመጡ /አመጣቸው ዘንድ ወድጀ ነበር፤ ነገር ግን ከእንቅልፋቸው ሊነሱ አልቻሉም።

ካህን:
ሶፍያ, ኢይደልወኪኑ ትንሥእዮሙ ለደቂቅኪ ኅበ ቤተ እግዚአብሔር?

አማርኛ፡
ሶፍያ፤ ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዘሻቸው ትመጪ ዘንድ ይገባሽ አልነበረምን?

ወ/ሮ ሶፍያ፡
 አአምር አቡየ; አላ ውእቶሙ ኢፈቀዱ ከመ ይምፅኡ (ኢፈቀዱ ይምፅኡ) ኅበ ቤተ ክርስቲያን ምስሌየ

አማርኛ፡
አውቃለሁ አባቴ፤ ነገር ግን እነሱ ከእኔ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጡ ዘንድ አልወደዱም።
ካህን፡
ወአነ አአምር!
ሰላመ እግዚአብሔር የሀሉ ምስሌኪ ወሑሪ በሰላም
አማርኛ፡
እኔም አውቃለሁ! የእግዚአብሔር ሰላም ከአንቺ ጋር ይሁን በሰላም ሂጂ/በሰላም ግቢ።
ወ/ሮ ሶፍያ:
አሜን አቡየ!
ወአንተሰ እቱ ኀበ ቤትከ በሰላም
አማርኛ፡
አሜን/ይሁን ይደረግ አባቴ፤ አንተም በሰላም ወደ ቤትህ ግባ።