Sunday, December 23, 2018

የግእዝ ቋንቋ፡ የመጀመሪያው የሰብአዊ ፍጡር ቋንቋ/Ge'ez Language: The First Language of Hu...



“ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን” ስለግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ታሪክ ነው።
የግእዝ ቋንቋ የመጀመሪያው የሰብአዊ ፍጡር ቋንቋ ነው ወይስ አይደለም?
“ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን” የተሰኘውን የግእዝ ቋንቋ መማርያ መጽሐፌን ለመግዛት ይህንን ይጫኑ

https://amzn.to/2WUPz3x 

አንድን ነገር ነው ወይም አይደለም ለማለት፤ የአንድን ታሪክ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የምንጠቅሰው አንዱ የጽሁፍ
ማስረጃ ቢሆንም የጽሁፍ ማስረጃ ብቻ ግን አይደለም፤ ነገር ግን ቡዙ ሌሎች መንገዶችም አሉ።
ከነዚህም መካከል፡
·       
ስለ ወቅቱ በቃል የሚነገሩና
እየተያያዙ የመጡ፤
·       
ተጓዳኝ የሆኑ ሌሎች ታሪኮችን
በማመሳሰል፤
·       
በወቅቱ ሰዎች ሲጠቀሙባቸው የነበሩ
ቁሳቁሶች፤ አባባሎች ወዘተ ይገኙበታል። ስለዚህ እኛም ስለግእዝ
ቋንቋ ስንነጋገር ስያሜውን፤ ትርጉሙን፤ የሰጠውን አገልግሎትና በሰዎች
ዘንድ ያለውን ሲያያዝ የመጣ ተጨባጭ ታሪክ
(በቃልም ቢሆን) ወዘተ አብረን እናያለን።

ለማነኛውም በመጀመሪያ “ግእዝ” ስለሚለው ቃል ወይም ስለ ስያሜው፤
እንነጋገራለን
ስያሜና ትርጉም

“አግአዘ” ነፃ አወጣ ከሚለው ግእዛዊ ግሥ “ግእዝ”
የሚል ቃል ይወጣል ትርጉሙ “ነፃነት” ማለት ነው።
ግእዝ ይዘቱን መሠረት በማድረግ “መጽሔተ አእምሮ”
ተብሎ ይጠራል። የእውቀት መስተዋት
(እውቀትን ወይም ጥበብን የሚያሳይ) ማለት ነው። የግእዝ
ቋንቋ መዝገበ ቃላት መጽሐፍ “መጽሐፈ ሰዋስው መጽሔተ አእምሮ” የሚል ርእስ አለው።

1. 
ለመሆኑ የሰው ልጅ የሚግባባው
በአንድ ቋንቋ ብቻ ነበር ወይስ ብዙ ቋንቋዎች ነበሩት? ስለዚህ ጉዳይ
መጽሐፍ ቅዱስ
ምን ይላል?፤ ዓለማውያን ጠበብትስ (የቋንቋ ምሁራን) ምን ይላሉ? “ ወአሐዱ ነገሩ ለኵሉ ዓለም ወአሐዱ ቃሉ።

የዓለም ቋንቋዎች ቤተሰብ
Ethnology
ባለፈው እንደተነጋገርነው የቋንቋ ቤተሰቦች (ላንጉች ፋሚሊ) የሚባሉት በጣም ብዙ ዓይነት ናቸው ለምሳሌያህል።
·       
የሚባሉት ብዙዎች ናቸው
·       
ለምሳሌ
·       
ኢንዶ ኤብሮፒያን
·       
አውስትሮንኢዥያን
·       
አፍሮ አስያቲክ
·       
ኒሎ ሳሃራን
ወዘተ የሚባሉት ጥቂቶቹ ናቸው።
 የቋንቅው ቤተሰብ ወይም ላንጉች
ፋሊሊ ትልቁ አከፋፈል ሲሆን በውስጡ ደግሞ ብራንች ወይም ቅርንጫፍ በመባል ይከፋፈላሉ።
(የኛ የሰመቲክ ቋንቋ ቤተሰብ የሚባሉት በዚህ
ውስጥ ይመደባሉ ማለትም የአፍሮ አስያቲክ ወይም የኒሎ ሳሓራን ቋንቋ ቤተሰብ የሚባሉት
ቅርንጫፎች ናቸው)

 የመጀመሪያው
የሰው ልጅ ቋንቋ ከዛሬ ሁለት መቶ ሺህ እና አምስት መቶ ሺህ ዓመታት መካከል በነበሩት ዓመታ
200,000 years ago and 50,000 years ago በምስራቅ አፍሪካ ይነገር እንደነበር ፕሮቶ ላንጉች (proto-language) በማለት
የቋንቋ ምሁራን ይናገራሉ።

2. 
ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት የግእዝ
ቋንቋ እግዚአብሔር ፍጥረቱን የፈጠረበት የመጀመሪያ ቋንቋ ነው ለማለት ከሚሰጧቸው ምክንያቶች መካከል አንዱና ዋናው ምንድን ነው?

3. 
ግእዝ የመጀመሪያው የሰብአዊ
ፍጡር ቋንቋ ባይሆን ኖሮ ለምን የውጭ ዜጎች ይፈልጉታል፤ ለምንስ እንደ ቅዱስና በጣም ተፈላጊ ቋንቋ አድርገው ለምን ይቆጥሩታል?

4. 
የግእዝ ቋንቋ ከሌሎቹ የአገራችን
ቋንቋዎችና ከዓለምም ቋንቋዎች ተለይቶ በተለየ ብሔር ያለመጠራቱና ኢትዮጵያዊኛ እየተባለ በጠራቱ ምንን የሚያመለክት ይመስለዎታል?

የዓለማዊ ሳይንቲስቶች
ምስክርነት
Ethnology
ባለፈው እንደተነጋገርነው የቋንቋ ቤተሰቦች (ላንጉች ፋሚሊ) የሚባሉት
በጣም ብዙ ዓይነት ናቸው ለምሳሌያህል።
·       
የሚባሉት ብዙዎች ናቸው
·       
ለምሳሌ
·       
ኢንዶ ኤብሮፒያን
·       
አውስትሮንኢዥያን
·       
አፍሮ አስያቲክ
·       
ኒሎ ሳሃራን
ወዘተ የሚባሉት ጥቂቶቹ ናቸው።
 የቋንቅው ቤተሰብ ወይም ላንጉች
ፋሊሊ ትልቁ አከፋፈል ሲሆን በውስጡ ደግሞ ብራንች ወይም ቅርንጫፍ በመባል ይከፋፈላሉ። (የኛ የሰመቲክ ቋንቋ ቤተሰብ የሚባሉት
በዚህ ውስጥ ይመደባሉ ማለትም የአፍሮ አስያቲክ ወይም የኒሎ ሳሓራን ቋንቋ ቤተሰብ
የሚባሉት ቅርንጫፎች ናቸው)

 የመጀመሪያው
የሰው ልጅ ቋንቋ ከዛሬ ሁለት መቶ ሺህ እና አምስት መቶ ሺህ ዓመታት መካከል በነበሩት ዓመታ
200,000 years ago and 50,000 years ago በምስራቅ አፍሪካ ይነገር እንደነበር ፕሮቶ ላንጉች (proto-language) በማለት
የቋንቋ ምሁራን ይናገራሉ።

ታላቁ ሊቅ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት
ሕዲስ” በተሰኘው የቋንቋዎች መድበል ግእዝና እና አማርኛን ትግርኛን ሌሎቹንም የአገራችን ቋንቋዎች ሳይቀር ከእብራይስጥ፤ ከአረብኛ
ከግሪክኛ ቋንቋዎች ጋር በማመሳጠር ከምንጩ ከመነሻው የሚያስረዳ የቋንቋ መድበል ነው። እና ይህ መጽሐፍ በመግቢያው በገጽ 10 ላይ

“ የዓለም
ቋንቋ ሁሉ በየነገዱ ስም ሲጠራ ግእዝ ብቻ በራሱ ስም ብቻ ይጠራል” ግእዝ 1ኛ መጀመሪያ ማለት ነው፤
“የብሉይ መምህራን ይልቁንም የጀርመን ሊቃውንት እነ ሲዲ ጳውሎስ፤ መአልም ዮሐንስ የተባሉት “ ወኮነ ኵሉ ምድር አሐተ ከንፈረ ወአሐደ ነገር.. ያለውን ይዘው ግእዝ የአዳም
ቋንቋ ነው
ይላሉ”

“ወአሐዱ ነገሩ ለኵሉ ዓለም ወአሐዱ ቃሉ።” “ወይቤ እግዚአብሔር
ናሁ አሐዱ ዘመድ ውእቱ ኵሉ ወአሐዱ ነገሩ ወከመዝ አሐዙ ይግበሩ ወኢየኀድጉ ይእዜኒ ገቢረ ዘሐለዩ በልቦሙ።

“ንዑ ንረድ ወንዝርዎ ለነገሮሙ ከመ ኢይሳምዑ ነገሮሙ አሐዱ ምስለ
ካልኡ። ወዘረወ እግዚአብሔር ነገሮሙ ወዘረዎሙ ውስተ ኵሉ ገጸ ምድር ወኀደጉ እንከ ነዲቆታ ለይእቲ ሀገር ወለውእቱ ማኅፈድ”

= የዓለም ሁሉ ቋንቋ አንድ ንግግሩም አንድ ነበረ፤ ---- እግዚአብሔርም
አለ እንሆ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፤ ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ መሥራትን
አይተውም፤ ኑ እንውረድ አንዱ የሌላውን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው። እግዚአብሔርም ቋንቋቸውን ለያየ፤ ከዚያም
በምድር ፊት ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከዚያም በኋላ ከተማይቱንና ግንቡን መሥራትን ተዉ።
ስለዚህም ስሟ ባቢሎን ተባለ፤ እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ
ሁሉ ደባልቋልና፤ … ዘፍ. 11፡1

 “ዳግመኛም
የሐዲስ መምህራን፦ “ወአሐዙ ይንብቡ በልሳናት ካልኣት” ያለውን እና “ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር” ካለው አያይዘው “ልሳናት ካልኣት” ከተባሉት አንደኛው ግእዝ ነው፤ ከኢትዮጵያ ለፋሲካ በአል
የሄዱት ፈላሾችና አይሁድ የጰራቅሊጦስ ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስን ስብከት በግእዝ ቋንቋቸው ስለሰሙ አምነው ተጠምቀው ከ3ቱሺህ አርድእት/ተከታዮች
ተቆጥረዋል” ይላሉ።
የሐዋርያት ሥራ 2፤ መዝሙር 67፡31
እምነ አውደ ጥናት ዘግእዝ
“ልሣነ ግእዝ የጋራ ቋንቋችን”
በሰላም ያስተራክበነ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘአብጸሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት፤

Wednesday, December 12, 2018