Tuesday, December 23, 2014

Wishes

Merry Christmas And Happy Gregorian New Year
መልካም የልደት በአል እና የግሪጎርያን አዲስ ዓመት



“ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን፤
ሰላምም በምድር፣ ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ”
“Glory to God in the highest,
And on earth peace, ...
መልካም የልደት በአልና ደስታን የተመላ
የጎርጎርዮሳውያን አዲስ ዓመት እንዲሆንላችሁ፤
ልኡል እግዚአብሔር የወገኖቻችንንና የሁላችንንም
ሕይወት እንዲባርክ የዘወትር ምኞቴ ነው።
I wish you a Merry Christmas
And Happiest Gregorian New Year
May ALMIGHTY God Bless your life
And the life of your loved one!
See More

Sunday, December 21, 2014

Information about Awde Tinat

Good News!


Awde Tinat is now on Appstore please download and learn everything in on app
go to the following link to download
http://apps.appmakr.com/awdetinat

Friday, December 19, 2014

ግእዝ ክፍል 19

Learn Geez Language Part 19/የግእዝ ትምህርት ክፍል 19

ባለፈው ትምህርታችን በክፍል 18 ማለት ነው የቅኔ ተማሪዎች በመምህራቸው የተዘረፈላቸውን ቅኔ እየመላለሱ ሲያጠኑ አይታችሁ ወይም ተመልክታችሁ ነበር ። በዛሬው በክፍል 19 ደግሞ መምህሩ የተቀኙትን ቅኔ ለተማሪዎቻቸው ሲፈቱላቸው ወይም ሲተረጉሙላቸው እንደምታዩና እኔም በትርጉሙ ላይ ባብራርያ እንደ ምሰጣችሁ ቃል ገብቼላችሁ ነበር ። ስለዚህ በገባሁት ቃል መሠረት ይዠላችሁ ቀርቤያለሁ ማለት ነው።
ዛሬ የምታዩት ቅኔ ጉባዔ ቃና ይባላል። የመጀመሪያው የቅኔ ክፍል ነው። ይህ የመጀመሪያ የሆነው የቅኔ ክፍል ሁለት ቤቶች አሉት ። ማለትም ቅኔ እንደሚታወቀው  የሚቀርበው በግጥም መልክ ሲሆን በሰምና  በወርቅ ወይም በሁለት ወይም ከሁለት በላይ በሆኑ ምሥጢራዊ ትርጉሞች የተቀነባበረ ነው። ይህ ማለት ተደራራቢ አባባል አለው ማለት ነው። ዛሬ የምናየው ሁለት ስንኝ ያለውን ቅኔ ወይም ግጥም ነው።ለዚህም ነው ሁለት ቤት ያለው ማለት ሁለት ስንኝ ያለው ማለት ነው።
 በአሁኑ ደረጃችን የምናተኩረው በቅኔው ሕግና በሰምና ወርቁ ላይ ሳይሆን የግእዝን ቋንቋ በማጥናቱ ላይ ነው ።
አንድ ተማሪ እያነበበ መምህሩ ደግሞ ትርጉሙንና ሰምና ወርቁን ሲያብራሩ፤ ጥያቄም እየጠየቁ ተማሪዎቹ ማለት ነው ሲከራከሩ ታያላችሁ እኔ የማነብላችሁም ያንኑ ቅኔ ነው ነገር ግን በደንብ ላይሰማችሁና ግልጽ ላይሆንላችሁ ስለሚችል የበለጠ ላስረዳችሁ ስለፈለግሁ ብቻ ነው። መልካም ትምህርት!


ጉባዔ  ቃና
1.    ኃያል ስምኦን ዘጽጌ ድንግል ጸገየ
2.     70 (ሰብአ) እደወ አምጣነ ገንጰለ ማየ። ይኸ ነው ቅኔው፤፡
በድንግል አበባ ያበበ የሆነ ስምኦን ኃይለኛ ነው
(ምክንያቱም) ሰባ ሰዎችን ወደውኃ ገልብጦ ጥሏልና (ገልብጧልና)
የእያንዳንዱ ቃል ትርጉምና የሥራ ድርሻ
ኃያል = ኃይለኛ ማለት ነው
 የስምኦን ቅጽል (ገላጭ) አድጀክቲብ ሆኖ 
ግን ውእቱ የቢባለውን አንቀጽ በውስጡ በማስገኘት
 የዐረፍተ ነገሩ ማሠሪያ አንቀጽ ሆኗል።
በዚህ ሙያው ( ኃያል ውእቱን መርምሮ ማሠሪያ ተብሎ ይጠራል)
ስምኦን = ስም ሲሆን ሙያው የዐረፍተ ነገሩ ወይም የቅኔው ባለቤት
= “የ” ማለት ሲሆን አገባብ  ሆኖ ጸገየ የሚለውን ግሥ እንዳያስር ይጠብቃል
ጸጌ = አበባ ማለት ነውስም ሲሆን “በ”  የሚል አገባብ የወጣበት ነው
ወይም “በ” ን ያስገኘ ነው ( አገባብ የወጣበት ይባላ)
ድንግል = የተፈጥሮ ለውጥ ያልታየባት ወይም ያልታየበት፤ ጥብቅ፤ እንደ ተፈተረ ያለ፤
 (በክብረ ንጽሕያ ያለ) ወዘተ ማለት ሲሆን የሥራ ድርሻው ወይም
 በዚህ አረፍተ ነገር ላይ ያለው ሙያ የጽጌ ዘርፍ ይባላል
 (ሁለት ቃላት ሲናበቡ መጨረሻ ላይ የሚገኘው ቃል ከኋላው ላለው ቃል ዘርፍ ይባላል።
ለምሳሌ ቤተ ክርስቲያን ስንል ክርስቲያን የሚለው ቃል የቤት ዘርፍ ይባላል።
ጸገየ  ግሥ ነው ነገር ግን በአንድ ቅኔ ላይ ሁለት ግሥ ማሰር ስለማይችል በ “ዘ”
 ተጠብቋል ወይ  አበበ አበባ አወጣ በማለት እንዳያሥር ተከልክሏል



70 = በቁሙ ቁጥር ነው ሙያው የእደው ቅጽል ነው
እደወ (እደው) = ወንዶች ማለት ሲሆን
ሙያው የገንጰለ ተሳቢ ነው ዳይሬክት ኦብጀክት ይባላል
አምጣነ = እና ወይን “ና” ማለት ሲሆን አብይ አበባብ ነው
ገንጰለ = ገለበጠ ማለት ሲሆን በሙያው እንዳያሥር አምጣነ ከልክሎታል።
 አምጣነ የውደቀበት ተብሎም ይጠራል (በዚህ ዐረፍተ ነገር ላይ)
ማየ (ማይ) = ውሀ ማለት ሲሆን “ወደ” የሚል አገባብን ያስገኘ ነው።
ስለዚህ አገባብ የወጣበት ይባላል።

Tuesday, December 9, 2014

ግእዝ ክፍል18

በዚህ ቪዲዮ የምትሰሟቸውና የምታዩዋቸው ተማሪዎች በዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ የመምህራንና ቀሳውስት ማሰልጠኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ውስጥ የሚገኙ የቅኔ ተማሪዎች ሲሆኑ የቅኔው መምህር የዘረፉትን ቅኔ በቃላቸው ለመያዝ እየቀጸሉ ወይም እያጠኑ ነው የምታዩዋቸው።
ይህ የአጠናን ዘዴ በቅኔ ቤት ወይም በመንፈሳዊ ትምህርት ቤት አነጋገር ወይም ቋንቋ ቅጸላ ይባላል። ስለዚህ እየቀጸሉ ነው ሲባል እያጠኑ ነው ማለት ነው።
እያጠኑ ወይም እየቀጸሉ ያሉት መምህሩ የዘረፉላቸውን ቅኔ ነው። መዝረፍ ወይም ዘረፋ ማለት ደግሞ በቅኔ ቤት ቋንቋ ያለ ምንም ዝግጅት ወይም በቂ የዝግጅት ጊዜ በድንገት ሐሳብን አመንጭቶ ድርሰትን መድረስ ወይም በግጥም መልክ የተቀነባበረ  ተደራራቢ ትርጉምን የሚሰጥ ሥነጽሁፍን መፍጠር ማለት ነው።
ከዚህ ቅጸላ ወይም ጥናት በኋላ መምህሩ የዘረፈውን ቅኔ ወይም የደረሰውን ድርሰት በቃላቸው ሸምድደው ይይዛሉ ለዚህም ነው እየመላለሱ የሚያጠኑት።
ትርጉሙንም እርስ በርሳቸው እየተረዳዱ ለመተርጎም ይሞክራሉ፤ አገባቦችንና የቃላቱን አቀማመጥ በቅኔ ትምህርት ሕግ መሠረት የተቀመጡ መሆናቸውን ይመረምራሉ፤ ያልገባቸውንና ስህተት ነው ብለው የሚገምቱት ቃል ወይም አገባብ ካለም ለመጠየቅ ይዘጋጃሉ።
እናንተም ይህንን ቅኔ በቃላችሁ በመያዝ ወደ አማርኛ ለመተርጎም ሞክሩ ። በእያንዳንዱ ቃልና አገባብም ምርምር አድርጉ።
በሚቀጥለው ትምህርት ደግሞ መምህሩ የዘረፉትን ቅኔ አንድ ተማሪ በቃሉ እያነበበ መምህሩ ሲተረጉሙ እንሰማለን።

Wednesday, December 3, 2014

ግእዝ ክፍል 18 የክ. 17 ማብራርያ

የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ክፍል 18



ይህ ትምህርት  የክፍል 18 ትርጎምና ማብራርያ ነው።
በዚህ ዝግጅቴ
ሁለት የተለያዩ ትርጉሞችን በመጠቀም ክፍል 18ን ለማብራራት እሞክራለሁ ። በንቃትና በትጋት እንድንከታተል እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን። አሜን!
1ኛው የትርጉም ዓይነት “የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም” በቅደም ተከተላቸው የሚለው ሲሆን ይህ ትርጉም በቀላሉ “የቃላት ትርጉም” ሊባል ይችላል።
2ኛው የትርጉም ዓይነት “የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም” የሚለው የአተረጓጎም ዓይነት ደግሞ “የይዘት ትርጉም” ልንለው እንችላለን።
ይህ አተረጓጎም የቃላቱን መሠረታዊ ትርጉም ሳይለቅ አቀማመጣቸውን ሊቀይር ይችላል፤ ለአማርኛ አነጋገር ተስማሚ የሆነ የቋንቋ ውበትን በመጨመር አስተካክሎ የመፍታት ወይም የመተርጎም መንገድ ነው።
ይህ አተረጓጎም የትርጉም ባለሙያዎች የሚጠቀሙበት ትክክለኛ የአተረጓጎም መንገድ ነው። ይህ ማለት የቋንቋ ችሎታችን እያደገ በሄደ ቁጥር አንድን ቋንቋ ስንተረጉም ማለትም ለምሳሌ ከግሪክኛ ወደ አማርኛ መተርጎም ብንፈልግ የግሪከኛውን ትክክለኛ ትርጉም ሳንለቅ ለአማርኛ ተናጋሪዎች የሚገባና የአማርኛን ቋንቋ ስልት የተከተለ አድርገን ካልተረጎምነው ለሚያነቡት ሰዎች ግልጽ አይሆንም። ማለት ነው።
ከዚህ ቀጥለን በእግዚአብሔርበአዳም እና በሔዋን መካከል የተደረገውን ውይይት እና በእባብም ላይ ጭምር የተነገሩትን ርግማኖች እንሰማለን። በዚህ ጽሁፍ ላይ የገለጽኳቸው በዘፍጥረት መጽሐፍ በምዕራፍ 3 ከቁጥር 9 ጀምሮ እስከ 17 የተገለጹትን ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ሳይሆን አሳጥሬ ለመከታተል የሚያመች አድርጌ ነው ያቀረብኩት ሙሉውን ማየት ከፈለጋችሁ የግእዙን መጽሐፍ ቅዱስ መመልከት ትችላላችሁ።
አንድ ትኩረት ልታደርጉበት የሚገባችሁ ነገር ቢኖር “የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም” በቅደም ተከተላቸው በሚለው ትርጉም ስር ትርጉማቸውን የምገልጸው ከመስማት አልፋችሁ ተጨማሪ ምርምርን ወይም ፍለጋን በሚጠይቅ መልኩ ነው ።
ለምሳሌ፦ “አይቴ ሀሎከ አዳም?” የሚለውን ዐረፍተ ነገር ወይም ጥያቄ የምተረጉመው
·       አይቴ=የት
·       ሀሎከ= አለህ(ነህ)
·       አዳም=ሰም ወይም በቁሙ አዳም ማለት ነው እያልኩ ሳይሆን
·       የት
·       አለህ(ነህ)
·       በቁሙ(አዳም)
በማለት በዚህ መልኩ ነው።
 ስለዚህ “አለህ ወይም ነህ” የሚለው የአማርኛ ትርጉም የሚናገረው ስለየትኛው የግእዝ ቃል ነው? የሚለውን ለማወቅ የምትጠቀሙት መንገድ በቅደም ተከተሉ ብቻ ነው። ለምሳሌ ነህ የሚለው በ2ኛ ተራቁጥር(ቁጥርም ባይኖር ቅደም ተከተሉን ስናይ ማለት ነው) ስለሆነ  ከግእዙ ዐ/ነገር በ2ኛ ተራቁጥር ላይ የሚገኘው “ሀሎከ” የሚለው ቃል ስለሆነ ነህ የሚለው ትርጉም የ”ሀሎከ” ነው ማለት ነው።
ለጊዜው ትርጉም የማይሰጥና ግራ የሚያጋባ መስሎ ሊታያችሁ ይችላል የተወሰነ ጥረት ካደረጋችሁ በኋላ ግን ይገባችኋል እውቀትም የበለጠ ትጨምራላችሁ። ስለዚህ አሁን ቀጥታ ወደ ዋናው ክፍል በመግባት መተርጎም እንጀምራለን።

እግዚአብሔር፣ አዳም፤ ሔዋን፤ እና እባብ እግዚአብሔር ይቤሎ ለአዳም፡= እግዚአብሔር አዳምን አለው
“.. አይቴ ሀሎከ አዳም.. ?
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
የት፤ አለህ (ነህ) ፤ አዳም (በቁሙ ስም)
 የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
 “አዳም ሆይ የትነህ”? “ሆይ” የሚለው ቃል በዐረፍተነገሩ ላይ ባይኖርም ለቅርብ ወይም ለሁለተኛ መደብ የምንጠቀመው ተጨማሪ የቋንቋ ውበት ነው።
አዳም ይቤሎ ለእግዚአብሔር፡=አዳም እግዚአብሔርን አለው
“.. ሰማዕኩ ቃለከ እንዘ ታንሶሱ ውስተ ገነት ወፈራህኩ እስመ ዕራቅየ አነ ወተኀባእኩ.. ”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
ሰማሁ፤ ቃልህን፤ ስ፤ስትመላለስ፤ ውስጥ፤ ገነት፤ ፈራሁም፤ ሰለ፤(እና) እራቁቴን፤ እኔ፤ ተሸሸግሁ፤
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
 “በገነት ውስጥ ስትመላለስ ሰማሁ፤ እራቁቴን ስለሆንኩም ፍራሁና ተደበቅሁ ወይም (ተሸሸግሁ)
እግዚአብሔር ይቤሎ ለአዳም፡=እግዚአብሔር አዳምን አለው
“.. መኑ አይድዐከ ከመ ዕራቅከ አንተ እም ዕፅኑ ዘአዘዝኩከ ከመ ኢትብላዕ እምኔሁ በላእከ?.. ”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
ማን፤ ነገረህ፤ እንደ፤ እራቁትህን፤ አንተ (በቁሙ)፤ተክል፤(እንጨት፤ዛፍ፤) የ፤ ያዘዝኩህን፤ እንደ እንዳትበላ፤ ከሱ፤ በላህን?
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
እራቁትህን መሆንህን ማን ነገረህ? እንዳትበላ ካዘዝኩህ ከዚያ ፍሬ በላህን?
አዳም ይቤሎ ለእግዚአብሔር፡= አዳም እግዚአብሔርን አለው
“.. ብዕሲት እንተ ወሀብከኒ ምስሌየ ትንበር ይእቲ ወሀበተኒ ወበላእኩ-” *”ዘ” ስለሚለው አገባብ በሌላ ክፍል እንማረዋለን።

የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
ሴት፤ አንተ(በቁሙ) የሰጠኸኝ፤ ከእኔጋር፤ ትኖርዘንድ፤ እሷ፤ ሰጠቺኝ፤ ም፤ በላሁ(በላሁም)
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
ከእኔ ጋር ትኖር ዘንድ የሰጠኸኝ ሴት እሷ ሰጠቺኝና በላሁ(ሰጠቺኝ በላሁም)
እግዚአብሔር ይቤላ ለሔዋን፡=እግዚአብሔር ሔዋንን አላት
“.. ለምንት ገበርኪ ዘንተ?.. ”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
ለምን፤ አደረግሽ ፤ ይህንን
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
ለምን ይህንን አደረግሽ?
ብእሲት (ሔዋን) ትቤሎ ለእግዚአብሔር፡=ሔዋን (ሴትዮዋ) እግዚአብሔርን አለችው
“.. አርዌ ምድር አስፈጠተኒ ወበላእኩ.. ”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
አውሬ(እባብ) ምድር(መሬት) አሳሳተቺኝ፤ ም፤ በላሁ(በላሁም)
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
የምድር አውሬ(እባብ) አሳሳተቺኝ በላሁም፡
እግዚአብሔር ይቤሎ ለአርዌ ምድር፡=እግዚአብሔር እባብን(የምድር አውሬን) አለው
“.. እስመ ገበርኮ ለዝንቱ ግብር ርጉመ ኩን እምኵሉ እንስሳ ወእምኵሉ አራዊተ ምድር ወበ እንግድዓከ ሑር ወመሬተ ብላዕ..”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
እና(ስለ)፤ አደረግኸው፤ ይህንን፤ ሥራ፤ የተረገምክ፤ ሁን፤ ከ፤ ሁሉ(ከሁሉ)፤ እንስሳ፤ ም፤ከ፤ሁሉ(ከሁሉም) አውሬዎች፤ የምድር፤ በ፤ በደረትህ(በሆድህ) ሂድ፤ ም፤ መሬትን፤ ብላ፤
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
ይህንን ሥራ ሠርተተኸዋልና ከእንስሳት ሁሉ፤ ከምድር አራዊት ሁሉ (ተለይተህ) የተረገምክ ሁን፤ በሆድህም(በደረትህም) ሂድ፤ አፈርንም ብላ..
እግዚአብሔር ይቤላ ለሔዋን(ለብእሲት)፡= እግዚአብሔር ሔዋንን(ሴትዮዋን) አላት
“.. አብዝኆ(ብዙኃ) አበዝኆ ለኀዘንኪ ወለሥቃይኪ ወበጻዕር ለዲ..”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
ማብዛትን፤ አበዛዋለሁ፤ኃዘንሺን፤ ም፤ ሥቃይሺን፤ በጭንቅም፤ ውለጂ
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
ኃዘንሺንና ስቃይሺን አበዛዋለሁ በጭንቅም ትወልጃለሽ፤(ውለጂ)
እግዚአብሔር ይቤሎ ለአዳም፡=እግዚአብሔር አዳምን አለው
“.. እስመ ሰማዕከ ቃለ ብእሲትከ ወበላዕከ እም ውእቱ ዕፅ ባሕቲቱ ዘአዘዝኩከ ከመ ኢትብላዕ ርግምተ ትኩን ምድር…”
የቃል በቃል ወይም የቃላትና የአገባብ ትርጉም በቅደም ተከተላቸው፦
እና፤ ሰማህ፤ ቃልን፤ ሚስትህ፤ በላህም፤ ከ፤ እሱ፤ ተክል(ፍሬ) ብቻውን፤ የ፤አዘዝኩህን፤ እንደ፤ አትብላ፤ የተረገመች፤ ትሁን፤ ምድር(መሬት)
የዐረፍተ ነገር እና የይዘት ትርጉም፦
የሚስትህን ቃል ሰምተህ እንዳትበላ ካዘዝኩህ ከዚያ ተክል(ፍሬ) በልተሃልና መሬት በአንተ ምክንያት የተረገመች ትሁን(ከአንተ የተነሣ)