Friday, October 30, 2015

የግእዝ ቋንቋ አሥራው ሆሄያት



Ge'ez Lesson for Beginers part 30/አሥራው






አሥራው ማለት ሥሮች ማለት ሲሆን ለነጠላ “ሥርው” ይሆናል ሥር ማለት ነው። ሥር ማለት ደግሞ መነሻ መጀመሪያ ማለት ነው።
አሥራው የሚባሉት የእርባ ግሥ ወይም የዘር ግሥ ሁሉ መነሻዎች ናቸው። ቁጥራቸው 4 ሲሆኑ
1.     
2.    
3.    
4.    
የሚባሉት ናቸው። እነዚህ ሆሄያት የግሥ ባዕድ መነሻዎች ይባላሉ።

ከትንቢት አንቀጽ በላይ አይወጡም ከትዕዛዝ አንቀጽ በታችም አይወርዱም። ስለዚህ በትንቢት፤በዘንድ፤ እና በትዕዛዝ አናቅጽ በሦስቱ ብቻ ይገኛሉ። ባዕድ በመባል የሚጠሩበት ምክንያትም

ምሳሌ፦ “አእመረ” ይህ መሠረታዊ ግሥ ነው፤ 4 ሆሄያትን ይዟል፤ (አ፤እ፤መ፤ረ) እነዚህ አራት ሆሄያት ሦስት ሊባሉም ይችላሉ ምክንያቱም “አ” እና “እ” የአንድ ሆሄ ዘር ስለሆኑ በ”አ” ዘር ይጠቃለላሉ።

 ስለዚህ “አእመረ” የሚባለው ግሥ ወይም አንቀጽ 3 የተለያዩ ሆሄያትን ይዟል 4ኛው ግን ከሦስቱ ውስጥ የአንዱ ዘር ነው። ልብ አድርጉ አሁን አእመረ የሚለውን ግሥ በምንገሥ ወይም በምናረባው ጊዜ ከጠቀስናቸው ሦስት የተለያዩ ሆሄያት ውስጥ ያልነበረ ወይም የሦስቱ ዘር ያልሆነ ሆሄ ወይም ፊደል ካየን ያ ሆሄ ወይም ፊደል “ባዕድ” ይባላል። ባዕድ ማለት ዘመድ ያልሆነ ማለት ነው። በሌላ አባባል ከመሠረታዊው ግሥ ውስጥ ከሚገኙት ሆሄያት ጋር የማይዛመድ ማለት ነው።

 አሁን ግሡ ሲረባ እንመልከት የሚከተሉት 4 ግሦች ወይም አንቀጾች በተደጋጋሚ እንደተነጋገርነው አበይ አናቅጽ ይባላሉ። ታላላቅ ግሦች ማለት ነው። 1ኛው “ሐላፊ አንቀጽ” ወይም “ቀዳማይ አንቀጽ”፤ 2ኛው፤ “ትንቢት አንቀጽ” ወይም “ካልአይ አንቀጽ”፤ 3ኛው “ዝንድ አንቀጽ” ወይም “ሣልሳይ አንቀጽ”፤ 4ኛው “ትእዛዝ አንቀጽ” ወይም “ሣልሳይ አንቀጽ”[1]  ይባላሉ።
1.      እመረ
2.   የአምር
3.   ያእምር
4.   ያእምር
 ወይም አምር ) የመጀመሪያዎቹ ሆሄያት ማለትም  “የ”  እና “ያ” ባዕድ ሆሄያት ናቸው
ከዚህ በላይ ያሉትን 4 አበይት አናቅጽ ስንመለከት መሠረታዊው ግሥ 4 ሆሄያት ወይም 2 የተለያዩ፤ 2 ተመሳሳይ ሆሄያት በድምሩ 4 ሆሄያት አሉት እነዚህም = አ፤ እ፤ መ፤ ረ፤ የተባሉት ሲሆኑ “አ” እና “እ” የአንድ አይነት ፊደል ዘሮች ስለሆኑ እንደ አንድ እንደሚቆጠሩ ተነጋግረናል። ስለዚህ ከመሠረታዊ ግሥ የተለየ እንግዳ ሆሄ በግሡ ላይ ከተጨመረ “ባዕድ” ይባላል ብለናል። “ባዕድ ሆሄ”ን መጨመር ደግሞ የትንቢት፤የዘንድ፤ እና የትእዛዝ አናቅጽ” መለያ ባሕርይ ነው።

 ስለዚህ “የአምር” ሲል “የ” የተባለ ከመሠረታዊው ግሥ ከ”አእመረ” ውስጥ ያልነበረ ሆሄን እናያለን ስለዚህ ይህንን ሆሄ “ባዕድ”[2] እንለዋለን ማለት ነው።
“ይ” በሦስት አናቅጽ
·         በአንድ ወንድ፤
·         በብዙ ወንዶች፤
·         በብዙ ሴቶች በኀላፊ አናቅጽ ውስጥ ይገኛል።
ምሳሌ፦ ግሡ “ሖረ” ቢሆን ለአንድ ሩቅ ወንድ
ሐውር፤ ሑር፤ይሑር

“ሖሩ” ለብዙ ወንዶች ለሩቆች
 ሐውሩ፤ ሑሩ፤ይሑሩ

“ሖራ” ለብዙ ሴቶች ለሩቆች
 ሐውራ፤ ሑራ፤ሑራ

“ት” በ5 አናቅጽ
1.      በቅርብ ወንድ፤
2.     ወንዶች፤
3.     ሴት፤
4.     ሴቶች፤ እና
5.     በአንዲቷ ሩቅ ሴት ይገኛል

ግሡ “ጸለየ” ቢሆን የቅርቡ ወንድ “ጸለይከ” ይሆናል ስለዚህ
ለቅርብ ወንድ
·         ጼሊ
·         ጸሊ
·         ጸሊ

ለብዙ ወንዶች ለቅርቦቹ በቅርቦቹ አናቅጽ በትእዛዝ አንቀጽ ላይ አሥራው አይገኙም
·         ጼልዩ
·         ጸልዩ
·         ጸልዩ
ለአንዲት ሴት ለቅርቢቱ
·         ጼልዪ
·         ጸልዪ
·         ጸልዪ

ለቅርቦቹ ብዙ ሴቶች
·         ጼልያ
·         ጸልያ
·         ጸልያ
ለሩቅ ሴት ለአንዷ
·         ጼሊ
·         ጸሊ
·         ጸሊ

“እ” እና “ን” በአንደኛ መደብ አናቅጽ ይገባል በሁለት ማለትም
በአነ እና በንሕነ አነ ለሚለው አንድ ነጠላ ለወንድም ለሴትም
·         ጸለይኩ
·         ጼሊ
·         ጸሊ
·         ጸሊ
ንሕነ ለሚለው ለብዙ ወንዶችም ሴቶችም
·         ጸለይነ
·         ጼሊ
·         ጸሊ
·         ጸሊ

ራብአቸውና ግእዛቸው የሚገኘው
በአድራጊ እና በአደራራጊ ግሦች፤ እንዲሁም “ሀ” እና “አ” በግሡ “መጀመሪያ”፤ “መካከል” ፤ እና “መጨረሻ ላይ ሲሆኑ ነው።

ምሳሌ፦ ግሡ “ቀተለ” ቢሆን አድራጊና አደራራጊ ግሦቹ “አቅተለ” እና “አስተቃተለ” የሚሉት ናቸው ስለዚህ

አንድ ሩቅ ወንድ አስደራጊ
·         ቅትል (“ት” ይጠብቃል)
·         ቅትል
·         ቅትል
አንድ ሩቅ አደራራጊ
·         ስተቃትል(“ት” ይጠብቃል)
·         ስተቃትል
·         ስተቃትል
በ”ሀ” እና በ”አ” ግሦች “አእመረ” በሚለው ግሥ ለአንድ ሩቅ ወንድ
·         አምር
·         እምር
·         እምር
ስለዚህ ሌሎችንም ግሦች በዚህ ዓይነት መልኩ ይሞክሩ።




Sunday, October 25, 2015

የመዝሙር ግጥሞች

የመዝሙር ግጥሞችን የሚፈልጉ ከሆነ አውደ ጥናትን በሚከተሉት መንገዶች ያነጋግሩ

Saturday, October 10, 2015

ግእዝ ክፍል 29

ትእዛዝ አንቀጽ


ትእዛዝ አንቀጽ ማለት ማዘዣ ወይም የማዘዣ ግሥ ፤ ትዕዛዝ የሚተላለፍበት ቃል ማለት ነው።
ትእዛዝ በቅጥራ የሚተላለፈው ከ1ኛ መደብ ወደ 2ኛ መደብ ሲሆን ቀጣ ባልሆነ መልኩ ግን በመልእክትና በመሳሰሉት ከ1ኛ መደብ በ2ኛ መደ በኩል ሌ3ኛ መደብ ይተላለፋል።

በልዋ ለእምየ ንኢ ኀቤየ

እኔ እናንተን “እናቴን እንድታዝዟት አዘዝኳችሁ
እንዲሁም ከ3ኛ መደብ በ1ኛ መደብ በኩል ለ2ኛ መደብ ይደርሳል።
“ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ  ለእለ ይትለአኩ”  ምልዕዎንኬ ለእላ መሳብክት ማየ”
ምሳሌ፡ለቀጥታ ትዕዛዝ ከ1ኛ መደብ ለ2ኛ መደብ
እኔ አንደኛ መደብ ነኝ፤
እናንተ ደግሞ 2ኛ መደብ ናችሁ፡

አጽምኡ ዘእቤለክሙ (አኃውየ ወአኃትየ!)

ምሳሌ 2፡ ቀጥታ ያልሆነ እና በታሪክ መልክ ከ1ኛ መደብ ለ2ኛ መደብ የሚነገር  ትእዛዝ፡
ቀጥታ ላልሆነ ትእዛዝ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን  በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ያለው  ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ  ለሠርግ አሳላፊዎች የተሰጠው ትእዛዝ ነው።
1.      ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ለእለ ይትለአኩ

2.   “ምልዕዎንኬ  ለእላ መሳብክት ማየ”

አንደኛውን ዐረፍተ ነገር የተናገረው ወንጌላዊው ነው
ሁለተኛውን ግን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ይህ ትእዛዝ በወቅቱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥዕሉ ላይ እንደምታዩት  በቀጥታ ያስተላለፈው ወይም የሰጠው ትእዛዝ ነው።

በኋላ ግን ወንጌላዊው በታሪክ መልክ “አላቸው” በማለት  በሓላፊ ግሥ  ነገረን።
ስለ ትእዛዝ አንቀጽ በሰፊው ማወቅ ከፈለጋችሁ  ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትሄዱ ሰዎች የቅዳሴውን ጸሎት በትኩረት ተከታተሉ።፡በተለይ ዲያቆናቱ የሚያስተላልፉ ወይም የሚናገሩት የጸሎት ክፍል የሚተላለፈው ቢያንስ 98 ከመቶው በትእዛዝ መልክ ነው።
ትእዛዝ አንቀጽ በሆሄያትና በድምጽ ወይም በአነጋገር በንባብ ከዘንድ አንቀጽ ጋር ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነው። መለየት የምንችለው  ከግሥ እርባታ ውስጥ ከሆነ “ትእዛዝ አንቀጽ” የሚገነው መጨረሻ ላይ ንው፤

በሥነ ጽሁፍ ውስጥ ከሆነ ግን መለየት የምንችለው በትርጉሙ ብቻ ነው።

ከግሡ መነሻ ላይ “ባዕድ ፊደላትን” ይጨምራል።
watch video about this topic