Saturday, October 10, 2015

ግእዝ ክፍል 29

ትእዛዝ አንቀጽ


ትእዛዝ አንቀጽ ማለት ማዘዣ ወይም የማዘዣ ግሥ ፤ ትዕዛዝ የሚተላለፍበት ቃል ማለት ነው።
ትእዛዝ በቅጥራ የሚተላለፈው ከ1ኛ መደብ ወደ 2ኛ መደብ ሲሆን ቀጣ ባልሆነ መልኩ ግን በመልእክትና በመሳሰሉት ከ1ኛ መደብ በ2ኛ መደ በኩል ሌ3ኛ መደብ ይተላለፋል።

በልዋ ለእምየ ንኢ ኀቤየ

እኔ እናንተን “እናቴን እንድታዝዟት አዘዝኳችሁ
እንዲሁም ከ3ኛ መደብ በ1ኛ መደብ በኩል ለ2ኛ መደብ ይደርሳል።
“ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ  ለእለ ይትለአኩ”  ምልዕዎንኬ ለእላ መሳብክት ማየ”
ምሳሌ፡ለቀጥታ ትዕዛዝ ከ1ኛ መደብ ለ2ኛ መደብ
እኔ አንደኛ መደብ ነኝ፤
እናንተ ደግሞ 2ኛ መደብ ናችሁ፡

አጽምኡ ዘእቤለክሙ (አኃውየ ወአኃትየ!)

ምሳሌ 2፡ ቀጥታ ያልሆነ እና በታሪክ መልክ ከ1ኛ መደብ ለ2ኛ መደብ የሚነገር  ትእዛዝ፡
ቀጥታ ላልሆነ ትእዛዝ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን  በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ያለው  ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ  ለሠርግ አሳላፊዎች የተሰጠው ትእዛዝ ነው።
1.      ወይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ለእለ ይትለአኩ

2.   “ምልዕዎንኬ  ለእላ መሳብክት ማየ”

አንደኛውን ዐረፍተ ነገር የተናገረው ወንጌላዊው ነው
ሁለተኛውን ግን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ይህ ትእዛዝ በወቅቱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥዕሉ ላይ እንደምታዩት  በቀጥታ ያስተላለፈው ወይም የሰጠው ትእዛዝ ነው።

በኋላ ግን ወንጌላዊው በታሪክ መልክ “አላቸው” በማለት  በሓላፊ ግሥ  ነገረን።
ስለ ትእዛዝ አንቀጽ በሰፊው ማወቅ ከፈለጋችሁ  ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትሄዱ ሰዎች የቅዳሴውን ጸሎት በትኩረት ተከታተሉ።፡በተለይ ዲያቆናቱ የሚያስተላልፉ ወይም የሚናገሩት የጸሎት ክፍል የሚተላለፈው ቢያንስ 98 ከመቶው በትእዛዝ መልክ ነው።
ትእዛዝ አንቀጽ በሆሄያትና በድምጽ ወይም በአነጋገር በንባብ ከዘንድ አንቀጽ ጋር ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነው። መለየት የምንችለው  ከግሥ እርባታ ውስጥ ከሆነ “ትእዛዝ አንቀጽ” የሚገነው መጨረሻ ላይ ንው፤

በሥነ ጽሁፍ ውስጥ ከሆነ ግን መለየት የምንችለው በትርጉሙ ብቻ ነው።

ከግሡ መነሻ ላይ “ባዕድ ፊደላትን” ይጨምራል።
watch video about this topic

No comments:

Post a Comment