Friday, October 1, 2021

የ2014/2022 ዓ/ም የግእዝና የአማርኛ ቋንቋዎች ትምህርት በአውደ ጥናት ዘግእዝ ምዝገባ ተጀምሯል!

ለግእዝና ለአማርኛ ትምህርት ይመዝገቡ!



በአውደ ጥናት ዘግእዝ ስለሚሰጠው የግእዝና የአማርኛ ተከታታይ ትምህርት አጭር ማብራርያ፤ ትምህርቱ በዋትስአፕና በዙም የቀጥታ ሥርጭት ይሰጣል፤ መማር የሚችሉትም ዕድሜያቸው ከ6 ዓመት በላይ የሆኑ ሕፃናትና አዋቂዎችም ጭምር ናቸው። የትምህርቱ ደረጃም ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ድረስ ይሰጣል።

የግእዝ መማርያ መጽሐፌንና ሌሎችንም መጻሕፍቶቼን አንዲሁም ልዩ ልዩ የሃይማኖት መጻሕፍትን ከአውደ ጥናት ለመግዛት የሚከተለውን ራሱ መጽሐፉን በመጫን ወደ አማዞን ገብተው ይግዙ። 

ከአማዞን መግዛት የማትችሉ በ+1 703 254 6601 በመደወል  አነጋግሩኝ በአድራሻችሁ ይላክላችኍል፤



Wednesday, September 29, 2021

 ምዝገባ ለግእዝና ለአማርኛ ቋንቋዎች

ትምህርት በአውደ ጥናት ተጀመረ!


የግእዝ ቋንቋ መማርያ መጽሐፌና ሌሎችንም መጻሕፍት ከአማዞን ለመግዛት የሚከተለውን መጽሐፉን ይጫኑ ወይም
ከአማዞን መግዛት የማይችሉ ከሆነ በ+1 703 254 6601 ደውለው ያነጋግሩኝ፤ I am directing you to amazon market place.

Sunday, May 16, 2021

የመጻሕፍት ትርጓሜ፡ አራተኛው የቤተ ክህነት ትምህርት ክፍል

የመጻሕፍት ትርጓሜ፥ አራተኛው የቤተ ክህነት የትምህርት ክፍል

የመጻሕፍት ትርጓሜ የሚባለው አራተኛው ክፍል ሲሆን በውስጡ አራት አበይት ክፍሎችን የያዘ ነው፡ እነሱም 
  • የብሉያት = 46 መጻሕፍት
  • የሐዲሳት = 35 መጻሕፍት
  • የሊቃውንት = 3 መጻሕፍት 
  • የመጽሐፈ መነኮሳት = 3 ክፍሎች ያሉት አንድ መጽሐፍ ትርጓሜ ዎች ናቸው፡
መጻሕፍት ለመግዛት የሚከተለውን ራሱ መጽሐፉን ይጫኑ ወደ አማዞን ይወስደዎታል፡ ከአማዞን መግዛት ካልቻሉ በ+1 703 254 6601 ይደውሉ በአድራሻዎ ይላክለዎታል

የትርጓሜ መጻሕፍት

ትርጓሜ መጻሕፍት የሚባለው የትምህርት ክፍል ከስያሜው እንደምንረዳው የቅዱሳት መጻሕፍትን ተደራራቢ ትርጉም እና ምሥጢር በማመሥጠርና በማራቀቅ ታሪካዊ ምንጫቸውንና ማስተላለፍ የሚፈልጉትን መንፈሳዊ መልእክት በመረዳት ማስረዳት ነው፤ የትርጓሜ መጻሕፍት ትምህርትን መማር የሚችለው የቅኔ ትምህርትን የተማረ ተማሪ ብቻ ነው።

ትርጓሜ መጻሕፍት የሚባለው የትምህርት ክፍል በአራት አበይት ክፍሎች ይከፈላል፤ እነሱም ከዚህ በታች በተራ በቅደም ተከተል የተጠቀሱት ናቸው።

1.  መጻሕፍተ ብሉያት - 46ቱ የበሉይ ኪዳን መጻሕፍት

2.  መጻሕፍተ ሐዲሳት - 35ቱ የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት

3.  መጻሕፍተ ሊቃውንት - ሐይማኖተ አበው፣ ፍትሐ ነገሥት፣ አቡሻክር (ባህረ ሐሳብ)

4.  መጻሕፍተ መነኮሳት - ማርይሳቅ፣ ፊልክስዮስ፣ አረጋዊ መንፈሳዊ

በነዚህ የትምህርት ደረጃዎች ሁሉ መምህራኑ የእምነትን የገብረ ገብነትን እና የትህትናን ባጭሩ የመልካም ሥነ ምግባርን ትምህርት ያስተምራሉ። እነዚህም

·        ፈሪሀ እግዚአብሔርን- እግዚአብሔርን መፍራት

·        ኀፊረ ገጽን - ታላላቆችን ማክበርና በአክብሮት መፍራት

·        አትሕቶ ርእስን - በታላላቆች ፊት በትህትና ራስን ዝቅ አንገትን ደፋ ማድረግ

·        ገቢረ ሠናይ - መልካም ነገርን መሥራት ወይም ማድረግ ወዘተ ናቸው።

·        ምንጭ፡ “ትዝታዬ” መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ

የመጻሕፍትን ትርጓሜ ትምህርት የጀመሩት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት እንደሆኑ የመጻሕፍት ትርጓሜ ሊቃውንት ይተርካሉ።

 

ልዑል አምላክ ማስተዋሉን ያድለን

ከአውደ ጥናት ዘግእዝ